የኢትዮጵያውያን አይሁዶች ተቃውሞ ሠልፍ በእሥራኤል
ማክሰኞ፣ ጥር 1 2004ማስታወቂያ
በእሥራኤል ሀገር በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን አይሁዶች በዛሬው ዕለት ከሦስት ሰዓታት በፊት ባደባባይ የተቃውሞ ሠልፍ አካሄዱ። የሀይፋ ወኪላችን ግርማው አሻግሬ እንደገለጸልን፡ የኢትዮጵያውያኑ አይሁዳይያን ተቃውሞ ሠልፍ የተደረገው ኪርያት መላኺ በተባለች ከተማ ነበር። የተቃውሞ ሠልፉን ምክንያት እንዲያብራራልን እና ሠልፉ ቴል አቪብን በመሳሰሉት ትልቆቹ ከተሞች ሳይሆን ለምን በኪርያት መላኺ እንደተካሄደ ቀደም ሲል በስልክ ጠይቄው ነበር።
ግርማው አሻግሬ
አርያም ተክሌ
ነጋሽ መሃመድ