የኢትዮጵያና የደቡብ ኮርያ ግንኙነት
ማክሰኞ፣ ግንቦት 23 2008ማስታወቂያ
ፕሬዚዳንት ፓርክ መንግሥታቸዉ ጥቃትንና ጽንፈኝነትን ለመታገል ከአፍሪቃ ሃገራት ጋር እንደሚሰራም ገልፀዋል። ፕሬዚዳንት ፓርክ ደቡብ ኮርያ « የአፍሪቃ ወዳጅ » እንድትሆን እንደሚሰሩና የልማት ግንኙነትን በተመለከተ በንግድ በትምህርት እንዲሁም ባህላዊ ትስስር የአፍሪካ-ደቡብ ኮሪያን ግንኙነት ያሳድጋል የሚል ተስፋ የጣሉበትን ንድፍም ማቅረባቸዉ ይታወቃል። የረጅም ጊዜ ታሪክ ያላቸዉ ደቡብ ኮርያና ኢትዮጵያ በተለይ በፕሬዚዳንትዋ ጉብኝት ይበልጥ መጠናከሩ ነዉ የተመለከተዉ። ከ 65 ዓመት በፊት በኮርያ በነበረዉ ጦርነት ኢትዮጵያዉያን አርበኞች በመንግስታቱ ድርጅት ጦር ኃይል ሥር ተሳታፊ መሆናቸዉ ይታወቃል። የደቡብ ኮርያ መንግሥት ዛሬ ከ 65 ዓመት በኋላ እነዚህን አባት ጡረተኞች እየረዳ መሆኑም ነዉ የተነገረዉ። የአዲስ አበባዉ ወኪላችን የኮርያ ዘማች አርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንትን አነጋግሮ ዘገባ ልኮልናል።
ጌታቸዉ ተድላ ኃይለጊዮርጊስ
አዜብ ታደሰ
አርያም ተክሌ