1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአፍሪቃ ና የአውሮፓ የኤኮኖሚ ግንኙነት

ረቡዕ፣ ሚያዝያ 1 2006

በአሁኑ ወቅት የአፍሪቃና የአውሮፓ የኤኮኖሚ ግንኙነት አዲስ አቅጣጫ እንዲከተል ያስፈለገበት ምክንያትና ጥቅሙ ምንድነው ? የኤኮኖሚ ግንኙነቱ በሁለቱ ክፍለ ዓለማት የፖለቲካና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ላይስ ምን ዓይነት ተፅእኖ ያሳድራል ?ከኤኮኖሚው ዓለም የሚያነሳቸው ጉዳዮች ናቸው ።

https://p.dw.com/p/1BeU8
EU Afrika Gipfel in Brüssel Mohamed Ould Abdel Aziz und Herman Van Rompuy
ምስል Reuters

ባለፈው ሳምንት ብራሰልስ ቤልጂግ ውስጥ የተካሄደው አራተኛው የአፍሪቃ የአውሮፓ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ተነጋግሮ ውሳኔ ካሳለፈባቸው ጉዳዮች ውስጥ የሁለቱ ክፍለ ዓለማት የኤኮኖሚ ግንኙነት አንዱ ነበር ። የመሪዎቹ ጉባኤና እዚያው ብራስልስ የተካሄዱ ሌሎች ተጓዳኝ ስበስባዎች የሁለቱን ክፍለ ዓለማት የኤኮኖሚ አጋርነት ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር እንዲሁም ኤኮኖሚያቸውን ለማሳደግ የሚያስችሉ አቅጣጫዎችን በመተለም ተጠናቀዋል ። በአሁኑ ወቅት የአፍሪቃና የአውሮፓ የኤኮኖሚ ግንኙነት አዲስ አቅጣጫ እንዲከተል ያስፈለገበት ምክንያትና ጥቅሙ ምንድነው ? የኤኮኖሚ ግንኙነቱ በሁለቱ ክፍለ ዓለማት የፖለቲካና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ላይስ ምን ዓይነት ተፅእኖ ያሳድራል ? የብራሰልሱ ዘጋቢያችን ገበያው ንጉሴ በዛሬው ከኤኮኖሚው ዓለም ዝግጅት ከሁለቱ ክፍለ ዓለማት መሪዎች ጉባኤ ውሳኔዎችና መግለጫዎች ጋር እያገናዘበ የሚዳስሳቸው ጉዳዮች ናቸው ።

ገበያው ንጉሴ

ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ