የአፍሪቃ ሰላምና መረጋጋት ባለፉት 50 ዓመታት
እሑድ፣ ግንቦት 25 2005ማስታወቂያ
ባለፈው ሳምንት በፊት 50 አመቱን ያከበረው የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት የአሁኑ የአፍሪቃ ህብረት ከተመሰረተባቸው ዓላማዎች ውስጥ የአፍሪቃ አገራትን ሉዓላዊነት ፣ የግዛት አንድነትና ነፃነት ማስጠበቅ የአፍሪቃውያንን አንድነትና ትብብርን ማጠናከር ፣ ለተሻለ ህይወት ማብቃት ይገኙበታል ። የአፍሪቃ አገራት ሙሉ በሙሉ ከቅኝ ገዥዎችና ከነጭ ዘረኞች አገዛዝና ጭቆና መላቀቃቸውና አፍሪቃውያንም መቀራረባቸው ትልቁ የ 50 ዓመት ፍሬ ቢሆንም በአንፃሩ ድርጅቱ የአፍሪቃውያንን መብቶችና መሠረታዊ ነፃነቶች አለማስጠበቁ በዋነኛ ድክመትነት ይነሳል ። በአንዳንድ የአህጉሪቱ ክፍሎች እስካሁን ሰላምና መረጋጋት ማስፈን አለመቻሉም ከህብረቱ ዋነኛ ችግሮች ይደመራል ። በዚህ ረገድ ኮንጎ ሱዳን ሶማሊያ ሊቢያ ማሊ ና ሌሎች ሃገሮችም ተጠቃሽ ናቸው ። ባለፉት 50 ዓመታት የአፍሪቃ ሰላምና መረጋጋት እንዴት ይገመገማል ? ችግሮቹ ምን ነበሩ ? መፍትሄውስ ምንድነው ? 3 እንግዶችን አወያይተናል ። ሙሉ ውይይቱን እንድታዳምጡ እንጋብዛለን ።
ሂሩት መለሰ
ልደት አበበ
መስፍን መኮንን