1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአፍሪቃ ምጣኔ ሐብት

ሐሙስ፣ ግንቦት 2 2004

የአፍሪቃ ምጣኔ ሐብት እንደ ጎርጎሮሳዉያኑ አቆጣጠር በ2050 ሥለሚደርስበት ደረጃና ከዕድገቱ ሕዝቡ ሥለሚጠቀምበት ሁኔታ ያላቸዉን ምክርና አስተያየት ሰጥተዋል።አፍሪቃ ዉስጥ ከታየዉ እድገትም ሆነ ከተፈጥሮ ሐብት የአፍሪቃ ሕዝብ ተጠቃሚ አልሆነም።

https://p.dw.com/p/14syS
A view of one of the largest steel producing companies in South Africa's industrial site close to the industrial port of Saldanha bay, South Africa, Saturday, March 8, 2008. As world economy have been under sever pressure with falling American house and stock prices, South Africa is facing an added energy crisis.(ddp images/AP Photo/Schalk van Zuydam)
ምስል AP


አዲስ አበባ የተሰበሰቡት የአፍሪቃ የምጣኔ ሐብት አዋቂዎችና ባለሙያዎች የአፍሪቃ የምጣኔ ሐብት እድገትንና እድገቱ የሚኖረዉን ፋይዳ አንስተዉ ተወያተዋል።ተሰብሳቢዎቹ የአፍሪቃ ምጣኔ ሐብት እንደ ጎርጎሮሳዉያኑ አቆጣጠር በ2050 ሥለሚደርስበት ደረጃና ከዕድገቱ ሕዝቡ ሥለሚጠቀምበት ሁኔታ ያላቸዉን ምክርና አስተያየት ሰጥተዋል።ተሰብሳቢዎቹ እንዳሉት እስካሁን አፍሪቃ ዉስጥ ከታየዉ የምጣኔ ሐብት እድገትም ሆነ ከአፍሪቃ የተፈጥሮ ሐብት የአፍሪቃ ሕዝብ ተጠቃሚ አልሆነም።ታደሰ እንግዳዉ ከአዲስ አበባ ዝር ዝር ዘገባ አለዉ።

በተያያዘ ዘገባ የቀድሞው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ኮፊ አናን፣ የአፍሪቃ መንግስታት የአህጉሩ ዕድገት ቀጣይነት ያለው እንዲሆን ወጣቱን ትውልድ ማስተማር ይኖርባቸዋል አሉ። አናን ፤ አዲስ አበባ ውስጥ በመካሄድ ላይ ባለው የዓለም የኤኮኖሚ መድረክ ፣ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ነው፣ ይህን ማሳሰቢያ ያቀረቡት። 60 ከመቶ በላይ የሚሆነው የአፍሪቃ ህዝብ ፣ ዕድሜው ከ 30 ዓመት በታች ነው። በዕድገት ለመራመድ፤ አናን ፣ አፍሪቃውያን መንግሥታት፣ ለህዝባቸው ብልጽግናን ማስገኘት በሚያስችሉ ተግባራት ላይ ማትኮር ይገባቸዋል፤ የህዝብን ኑሮ የሚያሻሽሉ የማኅበራዊና የኤኮኖሚ መርኆዎችንም መቀየስ ይኖርባቸዋል ብለዋል። ነገ በሚደመደመው የ 3 ቀናት ጉባዔ፤ በመካፈል ላይ ካሉት ከ 700 በላይ ተሳታፊዎች መካከል፣ 8 የአፍሪቃ መሪዎችና የቀድሞው የብሪታንያ ጠ/ሚንስትር ጎርደን ብራውን ይገኙበታል።

ታደሰ እንግዳዉ

ነጋሽ መሐመድ

ሸዋዬ ለገሠ