የአፍሪቃ ሕብረት ጦር ኪስማዮ ገባ
ዓርብ፣ መስከረም 18 2005ማስታወቂያ
ሶማሊያ የሠፈረዉ የአፍሪቃ ሕብረት (አሚሶም) ጦር የአሸባብን የመጨረሻ ጠንካራ ይዞታ ኪስማዮን በከፊል መቆጣጠሩን አስታወቀ። ኬንያ መራሹ የአፍሪቃ ሕብረት ጦር ሥልታዊቷን የወደብ ከተማ ላለፉት ሁለት ሳምንታት በምድር፥ ባየርና በባሕር ሲያጠቃ ነበር። ዉጊያዉ ዛሬም ከተማይቱ ዉስጥ አይሎ ዉሏል። የኬንያ ጦር ቃል አቀባይ ኮሎኔል ሳይረስ ኦጉና ዛሬ ጠዋት ጦራቸዉ ከተማይቱን ከአሸባብ አስለቅቆ ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥሯል ብለዉ ነበር። ዛሬዉኑ ቀትር ላይ ግን ጦሩ የያዘዉ የከተማይቱን ገሚስ ብቻ መሆኑን አስታዉቀዋል።
«ከተማይቱ ዉስጥ ወታደሮች አሉን።ይሕ ለአሸባብ ከፍተኛ ዉድቀት ነዉ።ምክንያቱም ጥቃት የተከፈተባቸዉ ድንገት ነዉ።አካባቢን በተመለከተ ከተማይቱ ትልቅ ናት።በዚሕም ምክንያቱ ሁሉንም የከተማይቱን ክፍል አልያዝንም።ይሁንና አሸባብ ይቆጣጠራቸዉ የነበሩ ሥልታዊ አካባቢዎችን ይዘናል።»
ከተማይቱን ለመያዝና ላለማስያዝ በተደረገዉ ዉጊያ ሥለደረሰዉ ጉዳት እስካሁን በይፋ የተባለ ነገር የለም። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እንዳስታወቀዉ ኬንያ መራሹ ጦር ከተመይቱን ለመያዝ ጥቃት ከከፈተ ጀምሮ ከስድስት ሺሕ የሚበልጥ የከተማይቱ ነዋሪ ሸሽቷል።
ነጋሽ መሐመድ
ሂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ