1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአፍሪቃ ህብረት የሰላምና የጸጥታ ጥበቃ ምክር ቤት በኤርትራ ላይ የወሰደው ውሳኔ

ሰኞ፣ ግንቦት 17 2001

የምሥራቅ አፍሪቃ መንግሥታት የልማት ማህበር ኢጋድ የሶማልያን ሸማቂዎች ትረዳለች በሚላት ኤርትራ ላይ የጦር መሳሪያ ማዕቀብ እንዲጣል ባለፈው ሳምንት ያሳለፈውን ውሳኔ የአፍሪቃ ህብረት የሰላምና የጸጥታ ጥበቃ ምክር ቤት አጸደቀው።

https://p.dw.com/p/Hx1L
ምስል DW /Maya Dreyer

ኤርትራ የሶማሊያን መንግሥት ለመጣል የሚታገሉ እሥላም ዓማጺያንን በማስታጠቅና በማሰልጠን ትረዳሰች በሚል ነው የምትወቀሰው። ባለፈው ሳምንት የሚኒስትሮች ም/ቤት ስብሰባውን በአዲስ አበባ ያካሄደው ኬንያ፡ ዩጋንዳ፡ ጅቡቲ፡ ሱዳን፡ ኢትዮጵያና ሶማሊያ የሚጠቃለሉበት የምሥራቅ አፍሪቃ መንግሥታት የልማት ማሕበር ኢጋድ እንዳስታወቀው፡ ኤርትራ በጉዳዩ ተጠያቂ ናት።

ጌታቸው ተድላ/አርያም ተክሌ

ተክሌ የኋላ፣