የአዲስ አባበ ቀላል የባቡር ፕሮጀክት
ዓርብ፣ መጋቢት 12 2006ማስታወቂያ
የአዲስ አበባው ቀላል የባቡር ትራንስፖርት ፕሮጀክት በሚቀጥለው ዓመት የሙከራ ሥራውን እንደሚጀምር የኢትዮጵያ የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን አስታወቀ ። የኮርፖሬሽኑ የኦፐሬሽንና አገልግሎት አሰጣጥ ዘርፍ ምክትል ሥራ አስፈፃሚ ለዶቼቬለ እንደተናገሩት ከ10 ወራት በኋላ ሥራው ተጠናቆ የቀላል ባቡር ትራንስፖርት የሙከራ አግልግሎት ይጀመራል ። ኮርፖሬሽኑ በከተማዋ በመገንባት ላይ ባሉት ሁለት መስመሮች ማለትም በሰሜን ደቡብ ና በምስራቅ ምዕራብ መስመሮች በቀን ወደ 250 ሺህ መንገደኞች ለማጓጓዝ አስቧል ። ህብረተሰቡንም ሊከሰቱ ከሚችሉ አደጋዎች ለመጠበቅ ግንዛቤ የማስጨበጥ እቅድ አለ ።
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ሂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ