1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአውሮፓ ህብረት መስፋፋት

ዓርብ፣ ሐምሌ 17 2001

በስድስት አገራት የጋራ ፍላጎት ተጠንስሶ የአባላቱ ቁጥር አሁን 27 የደረሰው የአውሮፓ ህብረት ከአሁን በኃላ አዳዲስ አባላትን በሚቀበልበት መንገድ ላይ አባል ሀገራቱ የተለያዩ አቋም እንደያዙ ነው ።

https://p.dw.com/p/Iwuk

አንዳንድ ሀገራት እንደ ቱርክ የመሳሰሉ ረዘም ካለ ጊዜ አንስቶ የአባልነት ድርድር ላይ ያሉ ሀገራት ይታቀፉ ሲሉ አንዳንዶች በተለይም መስራቾቹ ቱርክን በሙሉ አባልነት መቀበል የለብንም የሚለውን ግትር አቋማቸውን በማራመድ ላይ ናቸው ። የአየርላንድን ህዝብ ይሁንታ የጀርመን የቼክ ሪፐብሊክንና የፖላንድን መሪዎች ፊርማ የሚጠብቀው የተሻሻለው የሊዝበኑ የአውሮፓ ህብረት ውል እስኪፀድቅ ድረስ የመስፋፋት ጉዳይ ለጊዜው የተገታም ይመስላል ።

ሂሩት መለሰ/አርያም ተክሌ