1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአዉሮጳ ሕብረት የስደተኞች መርሕ

ሐሙስ፣ ጥቅምት 28 2006

አንዳድ የመብት ተሟጋቾች ከሰወስት መቶ ሐምሳ በላይ ኤርትራዉያን ስደተኞች ወደ አዉሮጳ ለመሻገር ሲሞክሩ ላፑዱዛ አጠገብ በደረሰዉ የጀልባ አደጋ ሰምጠዉ ለመሞታቸዉ የአዉሮጳ ሕብረትን የስደተኞች መርሕ ተጠያቂ ያደርጋሉ

https://p.dw.com/p/1ADkj
Grenzen in Europa Symbolbild Europa-Schild mit Fragezeichen. Das Schild zeigt auf blauem Hintergrund die goldenen Sterne und ein weisses Fragezeichen in der Mitte
ምስል picture alliance/Romain Fellens

የላምፔዱዛዉ መዳራሻ የባሕር ላይ አደጋ፥ አሁንም የአዉሮጳ ሕብረት ፖለቲከኞችንና የመብት ተሟጋቾችን እያወዛገበ ነዉ።አንዳድ የመብት ተሟጋቾች ከሰወስት መቶ ሐምሳ በላይ ኤርትራዉያን ስደተኞች ወደ አዉሮጳ ለመሻገር ሲሞክሩ ላፑዱዛ አጠገብ በደረሰዉ የጀልባ አደጋ ሰምጠዉ ለመሞታቸዉ የአዉሮጳ ሕብረትን የስደተኞች መርሕ ተጠያቂ ያደርጋሉ።የአዉሮጳ ሕብረት አባል ሐገራት መሪዎች ለዉጪ ስደተኞች አዲስ መርሕ የሚያጠና ግብር-ሐይል ሰይመዋል።ትናንት ብራስልስ-ቤልጂግ ተሰብስበዉ የነበሩ የስደተኞች መብት ተሟጋቾች፥ ሙሕራንና የምክር ቤት እንደራሴዎች ግን የአዉሮጳ መንግሥታትን በድጋሚ ወቅሰዋል።ገበያዉ ንጉሴ ዝር ዝር ዘገባ አለዉ።

ገበያዉ ንጉሴ

ነጋሽ መሐመድ

ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ