የአካል ጉዳተኝነትና ትምህርት
ማክሰኞ፣ ኅዳር 16 2007ማስታወቂያ
አካለ-ጉዳተኛ ልጆችን ወይም ወጣቶችን ከሌሎች ጋር ቀይጦ አንድ ክፍል ዉስጥ የማስተማር ጥቅም ጀርመንን ጨምሮ በአብዛኛዉ ዓለም የሥነ-ትምሕርት ባለሙያዎችን እያነጋገረ ነዉ።ጉዳዩ የብዙዎችን ትኩረት ሥቦ ለዉይይት ከመቅረቡ፤ ጥቅሙም በሰፊዉ ከመነገሩ ከብዙ ዓመታት በፊት ኢትዮጵያ ዉስጥ ሥራ ላይ ዉሏል። አካታች ወይም integratedየማስተማር ሥልትን ኢትዮጵያ ዉስጥ የጀማሪዉ አዲስ አበባ የሚገኘዉ የጀርመን ቤተ-ክርስቲያን ትምሕርት ቤት ነዉ።አሁንም ቀጥሎበታል።የትምሕርት ቤቱ ዓላማ፤ የትምሕርት ሥርዓቱና የተማሪዎቹ አስተያየት የጤና እና አካባቢ ዝግጅታችን ትኩረት ነዉ። የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ዮሐነስ ገብረ እግዚ አብሔር አጠናቅሮታል።
ዮሐነስ ገብረ እግዚ አብሔር
ነጋሽ መሐመድ