የአካል ጉዳተኛ ህጻናትና የጤና ሥርዓቱ በኢትዮጵያ
ማክሰኞ፣ ጥቅምት 21 2010ማስታወቂያ
የጤና አገልግሎቱ ለኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ሕጻናት ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ ከተለያዩ አቅጣጫዎች ተገለጠ። በተለይ በትምህርቱ ዘርፍ መድረኩ ሊመቻችላቸው እንደሚገባም ተሰምሮበታል። ከሕጻናት ማሳደጊያ እስከ ዩኒቨርሲቲ ድረስ ለአካል ጒዳተኞች የጤና ሥርዓት በአዲስ መልክ እየተዘረጋ መሆኑም ተገልጧል። በኢትዮጵያዊ ዋና ሥራ አስኪያጅ የሚመራው የዓለም ጤና ድርጅት የጤና ሥርዓት ዝርዝር መሰረት ኢትዮጵያ ከ190 የዓለማችን የተለያዩ ሃገራት 180ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። የጤና ጥበቃ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አህመድ ኢማኖን እና በብሔራዊ አካል ጒዳተኞች ማኅበር ዋና ሥራ አስኪያጁ አቶ ማሞ ተሰማን በማነጋገር ቀጣዩን ዘገባ ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ አጠናቅሯል።
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ማንተጋፍቶት ስለሺ
ሸዋዬ ለገሰ