የአንድነት ፓርቲ አባላትና ሰማያዊ ፓርቲ
ማክሰኞ፣ ጥር 26 2007ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባለፈዉ ሳምንት ዕዉቅና የነፈገዉ የኢትዮጵያ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ባለሥልጣናት እና አባላት ሌለኛዉን ተቃዋሚ የፖለቲካ ማሕበር ሰማዊ ፓርቲን ተቀላቀሉ። የአንድነት የቀድሞ አፈ-ጉባኤ፤ ምክትል አፈ-ጉባኤና ሌሎች ባለሥልጣናት ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት የሠማያዊ ፓርቲ አባል በመሆን የጀመሩትን ትግል ይቀጥላሉ። ሌሎች የአንድነት ፓርቲ ባለሥልጣናትና አባላትም ሰማዊ ፓርቲን እንዲቀየጡ ጠይቀዋል። ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ጋዜጣዊ መግለጫዉን ተከታትሎት ነበር። አርያም ተክሌ አነጋግራዋለች።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ