1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአንድነት አባላት አቶ አንዷለምን መጠየቃቸው

ዓርብ፣ መስከረም 18 2005

በትንትናው እለት ወደ ቃሊቲ እስር ቤት የሄዱት የፓርቲው አባላት አቶ አንዷለምን ማነጋገር የቻሉት ጥቂት ከተጉላሉ በኋላ መሆኑንም ተናግረዋል።

https://p.dw.com/p/16HCP
Autor: Ludger Schadomsky Copyright: Ludger Schadomsky/DW Titel: Dr. Negasso Gidada Thema: Der ehemalige Staatspräsident und heutige Vize-Vorsitzender des Achtparteien-Oppositionsbündnisses „Medrek“ , Dr. Negasso Gidada, ist vor der Wahl ein gefragter Gesprächspartner Schlagwörter: Negasso Gidada, Medrek, Forum, Äthiopien 2010, Äthiopien Opposition, Ethiopia 2010, Wahl Äthiopien
ምስል DW

የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ አባላት የእድሜ ልክ እሥራት ተፈርዶባቸው ቃሊቲ እሥር ቤት የሚገኙትን የፓርቲያቸውን ከፍተኛ ባለሥልጣን አቶ አንዷለም አራጌን ለመጀመሪያ ጊዜ መጠየቅ መቻላቸውን አስታወቁ። በትንትናው እለት ወደ ቃሊቲ እስር ቤት የሄዱት የፓርቲው አባላት አቶ አንዷለምን ማነጋገር የቻሉት ጥቂት ከተጉላሉ በኋላ መሆኑንም ተናግረዋል። ዶቼቬለ ያነጋገራቸው የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ ኢንጅነር ዘለቀ ረዲ አቶ አንዷለም የመንፈስ ፅናት እንደሚታይባቸው አስታውቀዋል። አቶ አንዷለም የእድሜ ልክ እሥራት የተፈረደባቸው ባለፈው ሰኔ ነበር። ወኪላችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ዝርዝሩን ልኮልናል።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ሂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ