1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአትሌት ኃይሌ ገሥላሴ ጋዜጣዊ መግለጫ

ሐሙስ፣ ነሐሴ 19 2008

«ኢትዮጵያ በርዮው ኦሎምፒክ ማግኘት የሚገባትን ውጤት አላገኘችም»አትሌት ኃይሌ ገብረ ሥላሴ

https://p.dw.com/p/1JplP
Bildergalerie Sportler aus Afrika - Haile Gebrselassie
ምስል Getty Images

በኦሎምፒክ እና በተለያዩ ዓለም ዓቀፍ ውድድሮች በርካታ ድሎችን በማስመዝገብ የሚታወቀው አትሌት ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ኢትዮጵያ በርዮው ኦሎምፒክ ማግኘት የሚገባትን ውጤት አላገኘችም ሲል ቅሬታውን ገለፀ ። የዚህ ችግር መንስኤም የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደራሽን አሠራር መሆኑን ኃይሌ ከቀድሞ አንጋፋ አትሌት እና አሠልጣኛ ቶሎሳ ቆቱ ጋር ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ በሰሰጠው መግለጫ አስታውቋል ።በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ቶሎሳ ቆቱ ፣ ሌላው አብይ ችግር የአትሌቶች የቡድን ሥራ መቅረት እና የአትሌቶች እና የአሰልጣኞች መራራቅ መሆኑን ተናግረዋል ። ጋዜጣዊ መግለጫውን የተከታተለው የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ዝርዝሩን ልኮልናል ።

ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ

ኂሩት መለሰ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ