1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአሜሪካ ሶማሊያውያን ስጋት

ዓርብ፣ መስከረም 17 2006

በኬንያው የናይሮቢ ግዙፍ የገበያ ማዕከል ውስጥ አሸባብ የፈፀመው ጥቃት የአሜሪካንንና የኬንያን የፀጥታ ትብብር ይበልጥ እንደሚያጠናክር ይጠበቃል ። በሌላ በኩል በዚሁ ጥቃት ሶማሊያውያን አሜሪካውያን ተሳትፈዋል መባሉ በአሜሪካ የሚገኙ ሶማሊያውያንን ከፍተኛ ስጋት ውስጥ ከቷል ።

https://p.dw.com/p/19pY6
ምስል Reuters

በኬንያው የናይሮቢ ግዙፍ የገበያ ማዕከል ውስጥ አሸባብ የፈፀመው ጥቃት አሜሪካን ከሶማሊያና ከአሸባብ ጋር በተያያዘ የምታራምደውን የውጭ ፖሊሲ እንደገና እንድትመረምር ሳያደርጋት እንደማይቀር ተነገረ ። ጥቃቱ የአሜሪካንንና የኬንያን የፀጥታ ትብብር ይበልጥ እንደሚያጠናክር ይጠበቃል ። በሌላ በኩል በዚሁ ጥቃት ሶማሊያውያን አሜሪካውያን ተሳትፈዋል መባሉ በአሜሪካ የሚገኙ ሶማሊያውያንን ከፍተኛ ስጋት ውስጥ ከቷል ። አሜሪካን የሚገኙ ወደ አክራሪነት የተቀየሩ ሶማሊያውያንም አሜሪካን ውስጥ ጥቃት ሊፈጽሙ ይችላሉ የሚል ስጋት አለ ። የዋሽንግተን ዲሲው ወኪላችን በጉዳዩ ላይ የተለያዩ የፖለቲካ ተንታኞችን አነጋግሮ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል ።

አበበ ፈለቀ

ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ