የአሜሪካን ወታደሮች የአፍጋኒስታን ቆይታ መራዘም
ዓርብ፣ ጥቅምት 5 2008ማስታወቂያ
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ አፍጋኒስታን የዘመተው የአሜሪካን ሠራዊት ቆይታ መራዘሙን ትናንት አስታወቁ ። ከዚህ ቀደም እንደታሰበው የሥልጣን ዘመናቸው ከማብቃቱ በፊት የአሜሪካን ሠራዊት ከአፍጋኒስታን ጠቅልሎ ወደ ሃገሩ እንደማይመለስ ኦባማ ተናግረዋል ።ኦባማ እንዳሉት የወታደሮቹ ቆይታ የተራዘመው የአፍጋኒስታንን መንግሥት የሚወጋው ፅንፈኛው ታሊባን በሃገሪቱ መጠነ ሰፊ ጥቃቶችን እያደረሰ በመሆኑ ምክንያት ነው ።በአሁኑ ጊዜ በአፍጋኒስታን ከ9 ሺህ በላይ የዩናይትድ ስቴትስ ወታደሮች ይገኛሉ ።የዚህ ሠራዊት ቁጥር በጎርጎሮሳዊው 2017 መጀመሪያ ላይ ወደ 5500 ዝቅ ይደረጋል ተብሏል ።የሰሜን አትላንቲክ የጋራ መከላከያ ቃል ኪዳን ድርጅት በኦባማ ውሳኔ ተደስቷል ።የዋሽንግተን ዲሲው ዘጋቢያችን ናትናኤል ወልዴ ዝርዝር አገባ ልኮልናል ።
ናትናኤል ወልዴ
ኂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ