1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአልሸባብ ግስጋሴና የኢትዮዽያ ምላሽ

ሐሙስ፣ ግንቦት 5 2002

ኤልበርዴ ከኢትዮዽያ ድንበር ብዙም የማትርቅ የሰሜን ሶማሊያ ከተማ ናት። ደካማው የሶማሊያ መንግስት ለወታደራዊ ስልጠና የሚጠቀማት ቁልፍ ይዞታ ናት። ባለፈው ቅዳሜ በአልሸባብ እጅ ላይ ወደቀች።

https://p.dw.com/p/NN0S
ምስል AP

ኤልበርዴ ከኢትዮዽያ ድንበር ብዙም የማትርቅ የሰሜን ሶማሊያ ከተማ ናት። ሮይተርስ የአልሸባብ የጦር አዛዥን ጠቅሶ እንደዘገበው በኤልበርዴ የመንግስቱ ጦር የለም። አዛዡ ሼክ ሀሰን ሞ አሊም ታኮው እንደገለጹት አልሸባብ በከባድ መሳሪያ ከደበደባት ኤልበርዴ የመንግስቱ ጦር ብዙም አልቆየም። ወደ ኢትዮዽያ ድንበር ዘልቀው ገብተዋል ። የኤልበርዴን መያዝ የኢትዮዽያ መንግስት ተራ ፕሮፖጋንዳ ሲል አጣጥሎታል። የኮሚኒኬሽንስ ጽ/ቤት ምክትል ሃላፊ አቶ ሽመልስ ከማል አልሸባብን ለማግዘፍ ተብሎ የተፈበረከ ወሬ ብለውታል።

መሳይ መኮንን

ሂሩት መለሰ