የኖርዌዩ ጥቃትና ቀኝ አክራሪዎች በአውሮፓ19 ሐምሌ 2003ማክሰኞ፣ ሐምሌ 19 2003ባለፈው ሳምንት አርብ በኖርዌይ መዲና ኦስሎና ፣ ከመዲናይቱ 45 ሜትር ርቆ በሚገኝ ወደብ ላይ በአንድ የኖርዌይ ዜጋ በተፈፀመ ጥቃትና ግድያ የኖርዌይ ህዝብ በድንጋጤ እንደተዋጠ ነው ። ጥቃት አድራሹ ግለሰብ የቀኝ አክራሪዎችን አስተሳሰብ አራማጅ መሆኑም ከኖርዌይ አልፎ መላ አውሮፓን እያነጋገረ ነው ።https://p.dw.com/p/RcJGምስል dapdማስታወቂያ በሰዓታት ልዩነት በኖርዌይ መዲና ኦስሎና ፣ ኡቶያ በተባለችው ደሴት የደረሰው ድርብ ጥቃት በኖርዌይ ታሪክ ከ2 ተኛው የዓለም ጦርነት ወዲህ ተወዳዳሪ ያልተገኘለትም ተብሏል ። ይህ ዘግናኝ አደጋ የደረሰበት ፣ ዕለተ አርብ በጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጠር ሐምሌ 22 ማለትም ሐምሌ 15 ,2003 ዓም የኖርዌይ የሃዘን ቀን ሆኗል ። ሂሩት መለሰ ነጋሽ መሐመድ