1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የናይጀሪያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫና ገዥው PDP

ዓርብ፣ ሚያዝያ 7 2003

ናይጀሪያ ነገ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ታካሂዳለች ። ምርጫውን ገዥው ህዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ በእንግሊዘኛው ምህፃር PDP ለ4 ተኛ ጊዜ ማሸነፍ ይፈልጋል ።

https://p.dw.com/p/RIJZ
ምስል DW

በአሁኑ ምርጫ ግን ፓርቲው ማሸነፍ ሊከብደው እንደሚችል ነው የሚገመተው ። የናይጀሪያ የምርጫ ኮሚሽን ከእንግዲህ ወዲያ ማጭበርበርን በቸልታ እንደማይመለከተው አስታውቋል ። ባለፈው ቅዳሜ በተካሄደው የህዝብ እንደራሴዎች ምርጫ ፓርቲው የያዘውን የምክር ቤት መቀመጫ እንዲቀንስ ተገዷል ። እስከ ትናንት በስተያ በተደረገው የመራጮች ድምፅ ቆጠራ ውጤት መሰረት PDP እስካሁን ይዞት የቆየውን ሁለት ሶሶተኛ አብላጫ ማጣቱ አይቀርም ። ፓርቲው ክርስቲያኑን ፕሬዝዳንት ጉድላክ ጆናታንን ለውድድር ማቅረቡ ደግሞ እያነገገረ ነው ። በሌላ በኩል የዶቼቬለ የሃውሳ ቋንቋ ክፍል ባልደረባ ቶማስ መሽ እንደዘገበው የአሁኑ የናይጀሪያ ምርጫ ሂደት ከቀደመው ምርጫ ጋር በንፅፅር ሲታይ የተሻለ መሆኑ እየተነገረ ነው ።

ቶማስ መሽ

ሂሩት መለሰ