የሽብር ጥቃት
ረቡዕ፣ ጥቅምት 22 2010ማስታወቂያ
ትናንት ከሰዓት በኋላ ኒውዮርክ ውስጥ በተከራየው መኪና ሆነ ብሎ እግረኞች እና በቢስክሌት ሲጓዙ የነበሩ ሰዎችን ገጭቶ በገደለው ሰው ላይ የሚካሄደው ምርመራ መቀጠሉ ተዘገበ። የአሜሪካን የፌደራል ምርመራ ቢሮ በምህጻሩ የኤፍ ቢ አይ ሠራተኞች በዲቪ ሎተሪ ከኡዝቤክስታን ወደ አሜሪካን መግባቱ የተነገረውን የዚህን ግለሰብ መኖሪያ ቤት ዛሬ መፈተሻቸውን አሶስየትድ ፕሬስ ዘግቧል። የዛሬ 16 ዓመት በሁለት የመንገደኛ አውሮፕላኖች ተገጭቶ እንዳልነበረ ከሆነው እና በሺህዎች የተገመቱ ሰዎች ካለቁበት የቀድሞ የዓለም የንግድ ማዕከል መንትያ ሕንጻዎች አቅራቢያ ትናንት በተፈፀመው በዚሁ ጥቃት የ 8 ሰዎች ህይወት ጠፍቷል ፤ ቢያንስ 11 ሰዎች ቆስለዋል። የዋሽንግተን ዲሲው ወኪላችን መክብብ ሸዋ ዝርዝሩን ልኮልናል።
መክበብ ሸዋ
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ