የነዳጅ ፍለጋ ጥረት በኢትዮጵያ
ረቡዕ፣ ሚያዝያ 23 2005ማስታወቂያ
ኢትዮጵያ ውስጥ ከኦጋዴን እስከ ኦሞ ከኦሞ እስከ ጋምቤላ በአገሪቱ ደቡብ ፣ ምዕራብና ምሥራቃዊ አካባቢዎች ሰፊ የተፈጥሮ ጋዝና የነዳጅ ዘይት ሃብት ክምችት መኖሩና ይህን ሃብት ከከርሰ-ምድር ለማውጣት ጥረት መያዙም በየጊዜው ይነገራል። የውጭ ኩባንያዎችም ኮንትራት ለመያዝ በአገሪቱ ላይ ይበልጥ እያተኮሩ መሄዳቸው አዘውትሮ የሚታይ ነገር ነው። ሃብቱን አውጥቶ ጥቅም ላይ ለማዋል በተጨባጭ ምን እየተደረገ ነው፤ እስካሁን የታየ ፍሬስ አለ ወይ? በጉዳዩ አዲስ አበባ ውስጥ በእንግሊዝኛ ቋንቋ እየታተመ የሚወጣውን ፎርቹን የተሰኘውን ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ አቶ ታምራት ገ/ጊዮርጊስን አነጋግረናል።
መሥፍን መኮንን
ነጋሽ መሐመድ