የነቢልጌትስ ቢሮ
ማክሰኞ፣ ኅዳር 7 2008ማስታወቂያ
አሜሪካዊዉ ቱጃር ቢል ጌትስና ባለቤታቸዉ ሜሊንዳ ጌትስ በስማቸዉ የሠየሙት የርዳታ ድርጅት አዲስ አበባ ዉስጥ ፅሕፈት ቤት ከፈተ። ድርጅቱ ለበርካታ ዓመታት ኢትዮጵያን ሲረዳ ቢቆይም እስካሁን ድረስ ኢትዮጵያ ዉስጥ ፅሕፈት ቤት አልነበረዉም።ትናንት የተከፈተዉ ቢሮ ድርጅቱ የሚሰጠዉን ርዳታ በቅርብ ለማስተባባር ይረዳል ነዉ የተባለዉ። ግብረ-ሠናዩ ድርጅት ከዚሕ ቀደም ናጄሪያና ደቡብ አፍሪቃ ዉስጥ ፅሕፈት ቤቶች ያሉት ሲሆን የአዲስ አበባዉ አፍሪቃ ዉስጥ ሰወስተኛ መሆኑ ነዉ።ጌታቸዉ ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።
ጌታቸዉ ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ነጋሽ መሐመድ
አዜብ ታደሠ