የቻይና ግፊት በሱዳን17 የካቲት 2000ሰኞ፣ የካቲት 17 2000ቻይና በሱዳን ምዕራባዊ ግዛት ዳርፉር ያለዉ ሰብዓዊ ቀዉስ እልባት እንዲያገኝ በካርቱም መንግስት ላይ የሚገባትን ያህልና አላደረገችም በሚል ትተቻለች።https://p.dw.com/p/E0ZPቻይና በዳርፉርምስል APማስታወቂያይህን የሚያካክስ ተግባር ለመፈፀም በሚልም የልዑካን ቡድኗን ወደሱዳን ልካለች። የልዑካን ቡድኑ የካርቱም መንግስት በተጠቀሰችዉ የአገሪቱ ክፍል ከተመድና ከአፍሪቃ ህብረት የሚዉጣጣዉ ቅይጡ ሰላም አስከባሪ ኃይል እንዲሰማራ የሚያደርገዉን የማደናቀፍ ተግባር እንዲያቆም ጠይቋል። የዳርፉር አማፅያንም ለዉይይት እንዲቀመጡ ተማፅኗል።