የቴሌኮም ረቂቅ ህግ
ሐሙስ፣ ሐምሌ 5 2004ማስታወቂያ
በቅርቡ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀል ረቂቅ ህግ በግለሰቦች የኢንተርኔት የድምፅና የስልክ ግንኙነት ላይ ተፅእኖዎች ሊያደርግ ይችላል ሲሉ የመስኩ ባለሞያዎችና ዓለም ዓቀፍ ድርጅቶች ልዩ ልዩ አስተያየቶችን በመሰንዘር ላይ ናቸው ። መንግሥት በበኩሉ ህጉ የተረቀቀው በመስኩ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን ለመቆጣጠርና የዜጎችን የመረጃ ልውውጥ ደህንነት እንዲሁም የመንግሥትንና የህዝቦችን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ነው ይላል ። ተቃዋሚዎች ደግሞ መንግሥት ህጉን ያረቀቀው በአገር ደህንነት ሽፋን የዜጎችን መብት እየገደበና እየተቆጣጠረ የስርዓቱን ደህንነት ለማሰጠበቅ እንዲያመቸው ነው ሲሉ በመተቸት ላይ ናቸው ። የቴሌኮም ረቂቅ ህግ ያስከተለው ስጋትና ያሳድራል የተባለው ተፅእኖ የውይይታችን ርዕስ ነው
ሂሩት መለሰ