የተፈጥሮ አደጋዎች መከታተል
ማክሰኞ፣ ጥቅምት 30 2003ማስታወቂያ
በተፈጥሮ አደጋዎች የሚጠቁ አገራትም ከዕለት ወደዕለት ቁጥራቸዉ እየተበራከተ ነዉ። በኢንዶኔዢያ ከሳምንታት በፊት በሚራፒ ተራራ መፈንዳት የጀመረዉ እሳተ ጎሞራ፤ አከታትሎ መፈንዳቱን ቀጥሏል። ኢንዶኔዢያ ከተፈጥሮ አቀማመጧና ተያያዥ ምክንያቶች ጋ በተገናኘ ከፍተኛ የእሳተ ጎሞራ ክምችት የተሰባሰበባት እንደሆነች ባለሙያዎች ይናገራሉ። የሰሞኑ የሚራፒ ተራራ እሳተ ጎሞራ አካባቢዉን የምድር ሲኦል እንዳደረገዉ ነዉ የሚነገረዉ። ሄይቲም እንዲሁ የተፈጥሮ አደጋ ደጋግሞ ጉዳት እያደረሰባት መሆኑ ይታያል።
ሸዋዬ ለገሠ
አርያም ተክሌ