ፕሬዝዳንት ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማየር ፓርቲዎቹ ድርድር ይቀጥሉ ብለዋል።
ሰኞ፣ ኅዳር 11 2010ማስታወቂያ
የፓርቲው መሪ ክርስቲያን ሊንደር እንዳሉት በተደራዳሪዎቹ መካከል የእምነት መሰረት አልነበረም። የድርድሩ ውድቀት ላለፉት 12 አመታት ጀርመንን የመሩትን መራሒተ-መንግሥት አንጌላ ሜርክል ፈተና ውስጥ ጥሏቸዋል። ቀጥሎ የሚፈጠረው ነገር በግልፅ ባይታወቅም መራሒተ-መንግሥቷ አዲስ ምርጫ እንዲካሔድ የመወሰን ሥልጣን ካላቸው ፕሬዝዳንት ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማየር ጋር ተገናኝተዋል። የጀርመን ጋዜጦች ለድርድሩ አለመሳካት ተጠያቂው ክርስቲያን ሊንደር እና ፓርቲያቸው ናቸው ሲሉ ይደመጣል። ፕሬዝዳንት ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማየር ግን የፖለቲካ ፓርቲዎች በድርድራቸው እንዲገፉበት ጥሪ አቅርበዋል።
ይልማ ኃይለሚካኤል
እሸቴ በቀለ
አርያም ተክሌ