1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የተ.መ.ድ ጉባኤና የባራክ ኦባማ ንግግር

ረቡዕ፣ መስከረም 16 2005

ኦባማ ለጉባኤው ባሰሙት ንግግር በተለይ ኢራን የኒዩክልየር ጦር መሣሪያ ባለቤት እንዳትሆን አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል ። ሙስሊሞችን ባስቆጣው ፊልም ምክንያት በሙስሊም አገራት በሚገኙ የአሜሪካ ኤምባሲዎች ላይ የተሰነዘሩትን ጥቃቶችና የተከተሉትን አመፆችም በዲሞክራሲ ላይ ያነጣጠሩ በማለትም አውግዘዋል ።

https://p.dw.com/p/16EyF
U.S. President Barack Obama addresses the 67th United Nations General Assembly at the U.N. headquarters in New York September 25, 2012. REUTERS/Mike Segar (UNITED STATES - Tags: POLITICS)
ምስል Reuters

ኒውዮርክ ውስጥ በመካሄድ ላይ ባለው 67 ተኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጉባኤ የመንግሥታት መሪዎች ዛሬም ንግግር ማድረጋቸውን ቀጥለዋል ። ትንንት በድርጅቱ አመታዊ ጉባኤ መክፈቻ ስነ ስርዓት ላይ ንግግር ካደረጉት መሪዎች አንዱ የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ባራካ ኦባማ ናቸው ። ኦባማ ለጉባኤው ባሰሙት ንግግር በተለይ ኢራን የኒዩክልየር ጦር መሣሪያ ባለቤት እንዳትሆን አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል ። ሙስሊሞችን ባስቆጣው ፊልም ምክንያት በሙስሊም አገራት በሚገኙ የአሜሪካ ኤምባሲዎች ላይ የተሰነዘሩትን ጥቃቶችና የተከተሉትን አመፆችም በዲሞክራሲ ላይ ያነጣጠሩ በማለትም አውግዘዋል ። ዝርዝሩን የዋሽንግተ ዲሲው ዘጋቢኢችን አበበ ፈለቀ ልኮልናል ።

አበበ ፈለቀ

ሂሩት መለሰ

ሸዋዮ ለገሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ