የቡርኪና ፋሶ ወታደሮች ታጋቾችን አስለቀቁ
ቅዳሜ፣ ጥር 7 2008ማስታወቂያ
ትናንት በቡርኪና ፋሶ ዋና ከተማ ኡጋዱጉ በሚገኘው ስፕሌንዲድ ቅንጡ ሆቴል ላይ በአል-ቃዒዳ ታጣቂዎች በተፈጸመው ጥቃት እና እገታ 23 ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች መቁሰላቸው ተሰምቷል።ሟቾቹ የ18 ሀገራት ዜጎች ሲሆኑ የጸጥታ ኃይሎች ሆቴሉን ነጻ ለማውጣት በወሰዱት እርምጃ አራት ታጣቂዎች መገደላቸውን የጀርመን ዜና አገልግሎት ዛሬ ዘግቧል። እገታው ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀው ዛሬ ማለዳ ሲሆን ታግተው ከነበሩ ሰዎች መካከል ቢያንስ 33 መቁሰላቸው ተሰምቷል። ከአል-ቃዒዳ ጋር ግንኙነት ሳይኖራቸው አይቀርም የተባሉት ታጣቂዎች ወደ ስፕሌንዲድ ሆቴል ከማምራታቸው በፊት በአካባቢው በሚገኝ ካፑቺኖ የተሰኘ ምግብ ቤት ላይ የእሩምታ ተኩስ ከፍተው ነበር።
እሸቴ በቀለ
ልደት አበበ