1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የቡርኪና ፋሶ ወታደሮች ታጋቾችን አስለቀቁ

ቅዳሜ፣ ጥር 7 2008

የቡርኪና ፋሶ የጸጥታ ኃይሎች በአል-ቃዒዳ ታጣቂዎች የተያዘውን ሆቴል በማስለቀቅ 126 ታጋቾችን ነጻ አወጡ።

https://p.dw.com/p/1HejW
Burkina Faso Anschlag auf Splendid Hotel in Ouagadougou
ምስል Getty Images/AFP/A. Ouoba

ትናንት በቡርኪና ፋሶ ዋና ከተማ ኡጋዱጉ በሚገኘው ስፕሌንዲድ ቅንጡ ሆቴል ላይ በአል-ቃዒዳ ታጣቂዎች በተፈጸመው ጥቃት እና እገታ 23 ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች መቁሰላቸው ተሰምቷል።ሟቾቹ የ18 ሀገራት ዜጎች ሲሆኑ የጸጥታ ኃይሎች ሆቴሉን ነጻ ለማውጣት በወሰዱት እርምጃ አራት ታጣቂዎች መገደላቸውን የጀርመን ዜና አገልግሎት ዛሬ ዘግቧል። እገታው ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀው ዛሬ ማለዳ ሲሆን ታግተው ከነበሩ ሰዎች መካከል ቢያንስ 33 መቁሰላቸው ተሰምቷል። ከአል-ቃዒዳ ጋር ግንኙነት ሳይኖራቸው አይቀርም የተባሉት ታጣቂዎች ወደ ስፕሌንዲድ ሆቴል ከማምራታቸው በፊት በአካባቢው በሚገኝ ካፑቺኖ የተሰኘ ምግብ ቤት ላይ የእሩምታ ተኩስ ከፍተው ነበር።

እሸቴ በቀለ

ልደት አበበ