የቀጠለው የየመን ውዝግብ27 መጋቢት 2003ማክሰኞ፣ መጋቢት 27 2003የየመን ተቀናቃኝ ወገኖች ካለፈው የካቲት ወር ወዲህ የቀጠለውን የህዝብ ዓመጽ በድርድር እንዲያበቁ የባህረ ሰላጤ ሀገሮች የትብብር ምክር ቤት ያቀረበውን ሀሳብ የየመን መንግስት እና አንዳንድ ተቃዋሚ ወገኖች መቀበላቸውን አስታወቁ።https://p.dw.com/p/RFX5ምስል APማስታወቂያ ምክር ቤቱ መንግስት አስፈላጊውን ተሀድሶ እንዲያደርግ በተጨማሪ አሳስቦዋል። ካለፉት ሰላሳ ሁለት ዓመታት ወዲህ በስልጣን ላይ ያሉት ፕሬዚደንት አሊ አብዱላ ሳሌህ ከስልጣን እንዲወርዱ በመጠየቅ በሀገሪቱ ተቃውሞው አሁንም የቀጠለ ሲሆን በዛሬው ዕለትም ቢያንስ ሁለት ሰዎች መገደላቸው ተሰምቶዋል። ነቢዩ ሲራክ አርያም ተክሌ ሂሩት መለሰ