1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሾንኮራ አገዳ መሬት ግጭት 

Merga Yonas Bula
ሐሙስ፣ የካቲት 2 2009

በጥቅምት ወር 2009 ዓ/ም በኦሮሚያ ክልል በተካሄደው ተቃዉሞ በተለያዩ ከተሞች የእርሻ ቦታዎችና ፋብሪካዎች መቃጠላቸዉ ሲዘገብ ነበር።

https://p.dw.com/p/2XEjX
Äthiopien, Adama
ምስል DW/M. Yonas Bula

Conflict on Sugarcane Land - MP3-Stereo

የየአካባቢው ነዋሪዎች በተለይ የእርሻ መሬቶች ላይ የደረሱት የቃጠሎዎቹ መንስኤ በልማት ስም መሬት ከገበሬዎች ያለ በቂ ካሳ መወሰዱ መሆኑን ይገልፃሉ። በተቃዉሞዉ ወቅት ቃጠሉ ከደረሰባቸው መካከል የወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካን ለመመገብ የተተከሉት የሾንኮራ አገዳ እርሻዎች ይገኙበታል። የሾንኮራ ተክሎቹ በምስራቅ ሸዋ ዞን በአዳማና በቦሰት ወረዳዎች እንድሁም በአርስ ዞን ዉስጥ ደግሞ ዶዶታ ወረዳ ዉስጥ እንደምገኝ የፋብሪካዉ ስራ አስኪያጅ አቶ ቱሉ ለማ ጠቅሰው በአከባቢዉ መንግስት በኒልዮኖች የሚቆጠሩ ገንዘቦችን አፍስሶ የመስኖ መሰረተ ልማት እንደሰራ ለዶቼ ቬሌ ተናግረዋል።

የ25 ዓመት ወጣት የሆነዉ ይህ የአዳማ ነዋሪ የሾንኮራ እርሻዉ የተቃጠለዉ መሬቱ ከገበሬዉ በጉለበት ስለተወሰደበት ነዉ ይላል።

Äthiopien, Zuckeranbau in Adama
ምስል DW/M. Yonas Bula

ይሁን እንጅ የፋብርካዉ ስራ አስካያጅ አቶ ቱሉ ከገበሬዉ «የተወሰደ መሬትም የለም፣ የሚከፈልም ካሳ የለም፣ አሁንም መሬቱ የገበሬዉ ነዉ፣ ግብርም እየከፈለበት ያለዉ ገበሬዉ ነዉ» ይላሉ። ይልቁንስ አከባብዉ ዝናብ አጠር አከባቢ ስለሆነ አርሶ አደሩ ራሱ በመስኖ ቢያለማው የበለጠ ተጠቃሚ ይሆናል የሚል ህሳቤ ነበረ ይላሉ። በሶስቱም ወረዳዎች 32 የገበሬ ማሃብራት እንዳሉና እነዚህ ማህበራትም አንድ የሾንኮራ አገዳ አምራቾች ህብረት ስራ ማህበር እንዳላቸው ስራ አስኪያጁ ይናገራሉ።

ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተልኩ ነዉ፣ ገበሬዎቹንም ሆነ ልጆቻቸዉን አነጋግሬያለሁ የሚሉት እኝህ የአዳማ ነዋሪ ግን ስራ አስኪያጁ አለ ያሉት ስምምነት ቢኖርም ገበሪዎቹ የሚያገኙት ገቢ ግን  በጣም ጥንሽ ነዉ ይላሉ።

ይህ የተቃጠለ የሾንኮራ እርሻ ምን ደረጃ ላይ ይገኛል ለሚለዉ አቶ ቱሉ ሲመሊሱ፣ አርሶ አደሩ ራሱ ዳግም ወደ ተከላ እንደገባና ወደ ፊትም ለሚፈጠሩት ችግሮች ፋብሪካዉና የአምራቾቹ ማህበር እየተገናኙ አብረው ይሰራሉ ሲሉ ተናግረዋል ። የአከባቢዉ ነዋሪዎች ደግሞ አርሶ አደሩ ዳግም ተከላው ላይ የተሳተፈው ተገዶ እንጅ ወዶ አይደለም ይላሉ።

የወንጅ ሾዋ ስኳር ፋብርካ የሾንኮራ አገዳ ፍላጎቱ በመጨመሩ የእርሻ መሬቱን ወደ 6000 ሄክታር ለማሳደግ ማቀዱ ተዘግቦ ነበር። ከዚህም ዉስጥ 75 በመቶዉ በገበሬዎች እንደሚለማም ተጠቅሷል። የሾንኮራ አገዳዉ ቆረጣ ሲደርስም አንድ ኩንታል በ50 ብር ለመቀበል እቅድ እንደነበረዉ ተዘግቧል።

መርጋ ዮናስ

ሂሩት መለሰ