የሶማሊያ ጉዳይ ዉይይት
ማክሰኞ፣ ሰኔ 9 2007ማስታወቂያ
የሶማሊያን ወቅታዊ ፖለቲካዊ ሁኔታ የገመገመ የፖለቲከኞች፤ የግብረ-ሠናይ ድርጅቶች ተጠሪዎችና የምሁራን ዉይይት ባለፈዉ ሳምንት በርሊን ዉስጥ ተደርጎ ነበር።Brot für die Welt የተሠኘዉ የጀርመን ግብረ-ሠናይ ድርጅት ባዘጋጀዉ ዉይይት ላይ የሶማሊያ መንግሥት ተወካይ፤ የሶማሊያን ጉዳይ የሚያጠኑ፤ ሶማሊያ የሚሠሩና ሥለ ሦማሊያ የሚያማክሩ የሶማሊያ እና የጀርመን ምሁራን ተገኝተዋል።ከስብሰባዉ ተሳታፊዎች አንዳዶቹ ለሶማሊያ የርስ በርስ ጦርነት መባባስ ኢትዮጵያንና ዩናይትድ ስቴትስን በከፊል ተጠያቂ አድርገዋል።የበርሊኑ ወኪላችን ይልማ ሐይለ ሚካኤል ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።
ይልማ ሐይለ ሚካኤል
ነጋሽ መሐመድ