1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሶማሊያ እዉነትና የለንደን ጉባኤ

ረቡዕ፣ ሚያዝያ 30 2005

ጥሩዉ ትኩረት ለሶማሌዎች እንዲጠቅም የሶማሊያ ፖለቲከኞችና የልብ ደጋፊዎቻቸዉ ደቡብ ሶማሊያ፥ ሶማሊላንድ፥ ፑንትላንድ፥ ወዘተ እየተባለ አራት ቦታ የተሸራረፈችዉን ሐገር ለማቀራረብ ቢጥሩ፥ የዉጪዉን ግፊት በዘዴ እያለፉ ከጠመንጃዉ ዉጊያ ጎን ለጎን ድርድርን እንደአማራጭ ለመከተል ቢዘይዱ የተሻለ ዉጤት ማምጣቱ አይገድም

https://p.dw.com/p/18TAI
British Prime Minister David Cameron (L) looks on as Somali President Hassan Sheikh Mohamud (R) speaks during a press conference at the Foreign and Commonwealth Office in central London on May 7, 2013. British Prime Minister David Cameron warned that failure to support the rebuilding of Somalia will lead to 'terrorism and mass migration', as he opened an international meeting aimed at helping to end more than 20 years of conflict. Representatives of more than 50 countries and organisations were attending the London conference, which is co-hosted by Cameron and Somali President Hassan Sheikh Mohamud. AFP PHOTO/BEN STANSALL (Photo credit should read BEN STANSALL/AFP/Getty Images)
ካምሩንና ሐሰንምስል AFP/Getty Images

ያኔም ግንቦት ነበር።ግን 1901 (ዘመኑ በሙሉ እንደ ጎርጎሮሳዉያኑ አቆጣጠር ነዉ) የለንደን ቅኝ ገዢዎች የመሩና ያስተባበሩት እና የራሷ ብሪታንያ፣ የኢጣሊያና የኢትዮጵያ መሪዎች ወደ ሶማሊያ ያዘመቱት ጦር በሶማሊያ ፀረ-ቅኝ ገዢ ሐይላት ለሰወስተኛ ጊዜ ተሸነፈ።ያኔም ግንቦት ነበር።ግን 1936።የፋሽሥት ኢጣሊያ መሪ ቤኒቶ መሶሎኒ አዲስ የማረኳትን ኢትዮጵያን፣ከኤርትራና ከኢጣሊያ ሶማሊያ ጋር ቀይጠዉ «አፍሪካ ኦርየንታሌ ኢታሊያና» የሚባል ግዛት መመሥረታቸዉን አወጁ። ዘንድሮም ግንቦት ነዉ።2013።ጥንት ሶማሊያ ቅኝ እንድተገዛ የተወሰነባት ለንደን፣ የዛሬዋ ሶማሌያ እንዴትነትን፣ የወደፊት ጉዞዋ ወዴትነትን የሚበይኑ ሐይላትን ጉባኤ ታስተናግዳለች።ነገ። ጉባኤዉ መነሻ፣ የሶማሊያ እዉነት ማጣቃሻ፣ እድምታዉ መድረሻችን ነዉ፥-ላፍታ አብራችሁኝ ቆዩ።

የብሪታንያ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ዊልያም ሔግ ከአስር ቀን በፊት በሞቃዲሾ የብሪታንያ ኤምባሲ የተባለዉን ቅፅር ግቢ ሲከፍቱ እንዳሉት መንግሥታቸዉ የሶማሊያን የእስካሁንና ያሁን እዉነት ብቻ ሳይሆን የወደፊት ጉዞዋን እንዴትነትም ያዉቀዋል።

ሔግ ሥለ ሶማሊያ የወደፊት ጉዞ በጎነት የሰጡትን ተስፋ ገቢር ለማድረግ መንግሥታቸዉ ይሁን ተባባሪዎቹ በጀመሩት መቀጠል አለመቀጠላቸዉ በርግጥ ሲሆን ነዉ የሚታየዉ።ከአሥራ-ሥምንተኛዉ መቶ ክፍለ-ዘመን ጀምሮ ዓለምን የሚቆጣጠሩት የአዉሮጳና የአሜሪካ ሐያላን ሔግ እንዳሉት የተበታተነችዉን የጎስቋላ፣ ደካማይቱን ሶማሊያን ዓይደለም የድፍን ዓለምን ሁለንተናዊ ሒደት ባሻቸዉ ማሾሩ አይገዳቸዉም።

ከማንም እና ከምንም በላይ የራሱን ጥቅም የሚያስቀድመዉ ሐያል ዓለም በየሥፍራዉ እንደሚያደርገዉ ሁሉ የሶማሊያን የወደፊት ጉዞ የሚቀይሰዉም ጉዞዋና መድረሻዋ የሶማሌዎችን ፍላጎት ሥለሚያረካ ሳይሆን የሐያላኑን ጥቅም ሥለሚጠብቅና በሚጠብቅበት መልኩ መሆኑ አያከራክርም።

ሶማሊያ በተለይ አዲስ ቋሚ መንግሥት ከመሠረተች ወዲሕ በተቆጠሩት መቶ ቀናት ዉስጥ የምዕራቡን ዓለም ከፍተኛ ትኩረት መሳቧ አላከረከራም።ትኩረቱ ግን ጀርመናዊቷ የአፍሪቃ ቀንድ የፖለቲካ ተንታኝ አኔተ ቬበር እንደሚሉት ለሶማሊያ ሕዝብ ቢያንስ እስካሁን የተከረዉ የለም።

«ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ሶማሊያ በተለይም ሞቃዲሾ ዉስጥ በንቃት ሲንቀሳቀስ እናያለን።ቱርኮች ቤቶች ሲገነቡ፥ ሠብአዊ ርዳታ ሲያቀብሉ እናያለን።የጀርመንዋ አምባሳደር ሞቃዲሾ ዉስጥ የሹመት ደብዳቤያቸዉን ሲያቀርቡ እናያለን።ብሪታንያዎች፥አሜሪካኖችም ሞቃዲሾ ዉስጥና ወደ ሞቃዲሾ ሲመላለሱ እናያለን።በሌላ በኩል ግን ባለፉት መቶ ቀናት የታየዉ ሁሉ ለሶማሊያ ሕዝብ የጠቀመዉ የለም።»

ሔግ በቅርቡ የተናገሩትን ተስፋ እዉን ለማድረግ መንግሥታቸዉና ተባባሪዎቹ ከጣሩ የሚጥሩትም ለእነሱ እስከጠቀመና እስከፈለጉት ድረስ ብቻ ባይሆን ኖሩ የኤምባሲ ፅሕፈት ቤት ለመክፈት፣ ጉባኤ ለመጥራት፣ ሞቃዲሾ በድብቅም ቢሆን ለመመላለስ እና ገንዘብ ለማዋጣት ሃያ-ሁለት ዘመን ባልጠበቁ ነበር።

የዛሬዋ ሶማሊያ ለንደኖች ቅኝ ሊገዟት የዘመቱባት፣ ቅኝ የገዟትም አይነት አይደለችም።የዛሬዋ ሶማሊያ የለንደን መሪዎች በሁለተኛዉ የዓለም ጦርነት ወቅት የሮም ጠላቶቻቸዉን የመቱባት፣ ወይም በሺሕ ዘጠኝ መቶ ሥልሳዎቹ መጀመሪያ ነፃነቷን የፈቀዱላት አይደለችም።የዚያድ ባሬዋ ሶማሊያም አይደለችም።የሔግ ቀዳሚዎች ኤምባሲያቸዉን የዘጉባት፣ አክራሪዉ ደፈጣ ተዋጊ ቡድን አሸባብ የሚገዛት አይነትም አይደለችምም።

የዛሬዋ ሶማሊያ ሔግ እንደ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ባደራጁት፣ ዴቪድ ካሜሩን እንደጠቅላይ ሚንስትር በሚመሩት በነገዉ ጉባኤ ሠነድ እንደተጠቀሰዉ፥ የጎሳ መሪዎች የወከሉት ምክር ቤት የተሰየመባት፣ አዲስ ሕገ-መንግሥት የፀደቀባት፥ ቋሚ መንግሥት የተመሠረተባት ናት።የሶማሊያ ጉዳይ አጥኚ ረሽድ አብዲም ይሕን ይመሰክራሉ።

«ባለፈዉ አንድ ዓመት በርካታ ገንቢ ለዉጦች ታይተዋል።መንግሥት የሚቆጣጠራቸዉ አካባቢዎችን በማስፋፋቱ ረገድ ብዙ እመርታ ታይቷል።ያም ሆኖ በሶማሊያ ጦር ዉስጥ አሁንም የመዋቅርና የአደረጃጀት ችግር አለ።»

የፖለቲካ ተንታኙ እንዳሉት ሶማሊያ ከብዙ ችግሮቿም ጋር ቢሆን ዛሬ ከተሻለ ደረጃ መድረሷ እዉነት ነዉ።ከተሻለ ከሚባለዉ ደረጃ ለመድረሷ ከማንም፥ የዉጪ ሐያል ትልቁን እገዛ ያደረገዉ የአፍሪቃ ሕብረት ያዘመተዉ ጦር ነዉ።አሚሶም።የዩጋንዳ፥ የብሩንዲ፥የኢትዮጵያ በቅርቡ የኬንያ፥ የጅቡቲ እና የሌሎቹ የአፍሪቃ ሐገራት ወታደሮች ዛሬም ደም ሕይወታቸዉን እየገበሩ ነዉ።

የአፍሪቃ ወታደሮች ባይኖሩ ኖሩ ባለፉት መቶ ቀናት ከዋሽንግተን-እስከ ብራስልስ ብዙ የተነገረለት፥ አድናቆት፥ እዉቅና ድጋፉ የተንቆረቆረለት የፕሬዝዳት ሐሰን ሼኽ መሐሙድ መንግሥት ሳምንታት መቆየቱም ሲበዛ አጠራጣሪ ነዉ።ማርክ ፕላንክ ኢንስቲቱዩት የተሰኘዉ የጀርመን ጥናት ተቋም የምሥራቅ አፍሪቃ ጉዳይ አጥኚ ማርኩስ ሆነ እንደሚሉት አዲሱ መንግሥት የርዕሠ-ከተማ ሞቃዲሾን ፀጥታ እንኳን ማስከበር አልቻለም።

«እዉነቱን መናገር ከተፈለገ የሞቃዲሾ (አንፃራዊ) ፀጥታ እንኳን የተፈጠረዉ በአሚሶም ድጋፍ ነዉ።መንግሥት የራሱን ርዕሠ-ከተማ ፀጥታ እንኳን ለማስከበር የዉጪ ሐይላት ጥገኛ ነዉ።ምክንያቱም የራሱ ፀጥታ አስከባሪዎች ብቁ አይደሉም።»

የለንደኑ ጉባኤ አዘጋጆች እንዳሉት የነገዉ ጉባኤ ከሚመክርና ከሚወስንባቸዉ ርዕሶች ዋናዉ ረሺድ «የመዋቅርና የአደረጃጀት ችግር አለበት» ያሉት የሶማሊያ መንግሥት የፀጥታ ሐይል ነዉ።የጉባኤዉ አዘጋጆች እንዳሉት የፕሬዝዳት ሐሰን ሼኽ መሐሙድ መንግሥት ጦር ሐይሉን፥ ፖሊስ ሠራዊቱን፥ የፍትሕ ሥርዓቱን የሚያደራጅ፥ የሚያጠናክርበትን፥ የገንዘብ ወጪዉን ቅጥ የሚያሲዝበትን ዕቅድ ያቀርባል።

ሐምሳ ሐገራትንና እና ድርጅቶችን የሚወክሉት ጉባኤተኞች ደግሞ እነዚሕን ዕቅዶች ገቢር ለማድረግ የሚረዱበትን ሥልት ይነድፋሉ።እና የሶማሊያን የጉዞ አቅጣጫ ይወስናሉ።አክራሪዉ ደፈጣ ተዋጊ ቡድን አ-ሸባብ ትናንት ከሞቃዲሾ ያሥተላለፈዉ መልዕክት ግን ካሁኑ መላ ካልተበጀለት፥ የሶማሊያ የወደፊት ጉዞ እንደ እስካሁኑ ሁሉ ጨፍጋጋነቱን በግልፅ አመልካች ነዉ።የአሸባብ አጥፍቶ ጠፊዎች እንዳፈነዱት በታመነ-ቦምብ በትንሽ ግምት አስር ሰዉ ገድለዋል።

አሸባብ ከሁለት ሳምንት በፊት ሞቃዲሾ ላይ ባደረሰዉ ተመሳሳይ የቦምብ ጥቃት ከሰላሳ በላይ ሰዎች ገድሎ ነበር።ከዓለም አቀፉ አሸባሪ ድርጅት አል-ቃኢዳ ጋር ግንኙነት አለዉ የሚባለዉን አሸባብን ማጥፋት የፖለቲካ አዋቂ አብዲ ረሺድ እንደሚሉት እንዲሕ ባጭር ጊዜ የሚሳካ አይነት አይደለም።

«አደጋ ለመጣል በጣም የቆረጡ እና በቅጡ የተደራጁ አክራሪ ደፈጣ ተዋጊዎች አሉ።ሞቃዲሾ ዉስጥ ባለፈዉ የተፈፀመዉን ጥቃት፥ እንዳየነዉ በጣም አደገኛ ሁኔታ መኖሩን ጠቋሚ ነዉ።እና እኔ ከአሸባብ ጋር የሚደረገዉ ትግል ረጅም ጊዜ የሚጠይቅ ነዉ ብዬ እሰጋለሁ።»

የጠመንጃዉ ትግል ኢራቅና አፍቃኒስታን፥ ላይ ያመጣዉን ዉጤት አይተናል።እርግጥ ነዉ አሜሪካኖች የአልቃኢዳ ተባባሪ ይሏቸዉ ከነበሩት ከኢራቅ የሱኒ አማፃያን ጋር የተደራደሩት፥ የአፍቃኒስታኑ ፕሬዝዳት የሐሚድ ካርዛይ መንግሥት ከታሊባኖች ጋር እንዲደራደር ግፊት ማድረግ የጀመሩት የጠመንጃዉ ዉጊያ ከዕልቂት ዑደት ባለፍ የተከረዉ እንደሌለ በመረዳታቸዉ ነዉ።

የለንደኑ ጉባኤ የሶማሊያ መንግሥት ጦር ሐይሉን እንዲያደረጅ፥ እንዲያጠናክር ከማዘዝ ሌላ ከሶማሌዎች መሐል ከወጡት የሶማሊያ ሸማቂዎች ጋር እንዲደራደር በሐሳብ ደረጃ እንኳን አይጠቁምም። በጉባኤዉ ከተጋበዙ መሪዎች አንዱ ደግሞ አዲሱ የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሑሩ ኬንያታ ናቸዉ።

ኬንያታ በምዕራባዉያኑ ፍላጎትና ግፊት የተመሠረተዉ፥ የሚሠራዉና፥ የሚመማራዉ ዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት በሰዉ ልጅ ላይ በተፈፀመ ወንጀል የከሰሳቸዉ ፖለቲከኛ ናቸዉ።ግን ብሪታንያዎች የሚሉትን ከፈፀሙ፥ ብሪታኒያዎች ባዘጋጁት ጉባኤ ላይ እንዲገኙ በብሪታንያዎች ከተጋበዙ በወንጀል መጠርጠር፥ በትልቁ ፍርድ ቤት መከሰሳቸዉ፥ ምናልባት እንደተጠረጠሩት ሕዝብ አጫርሰዉም ከሆነ-ሁሉም የሚወሳ ጉዳይ አይደለም።

የብሪታንያ ቅኝ ገዢዎች በ1890ዎቹ ማብቂያ ወደ ዛሬዋ ሰሜን ሶማሊያ ብቅ ያሉት፥ ደቡብ ሶማሊያ ኢጣሊያኖች፥ ጀቡቲ ላይ ፈረንሳዮች መግባታቸዉን አይተዉ ቅኝ ግዛት ለመሻማት ነበር።ብሪታንያዎች ሰሜን ሶማሊያን ሙሉ ለሙሉ ለመያዝ ያደረጉት ተደጋጋሚ ሙከራ፥ ታዋቂዉ የሶማሊያ መሪ ሰይድ ኋላ ሙላሕ መሐመድ አብብደላሕ አል-ሐሰን በሚመሯቸዉ በሶማሊያ ፀረ-ቅኝ ገዢ ሐይላት በተደጋጋሚ ከሽፎባቸዋል።

የለንደን ገዢዎች ተደጋጋሚዉን ሽንፈት ለመበቀል ከተሻሚዎቻቸዉን ከኢጣሊያኖችን፥ ጋር ተወዳጅተዉ፥ ኢጣሊያኖችን አድዋ ድል የመቷቸዉን ኢትዮጵያዉያንን አባብለዉ የሙላሑን ሐይላት ዳግም ገጠሙ።ኮሎኔል ኢ.ጄ ስዋይን የመሩና ያስተባበሩት የብሪታንያ፥የኢጣሊያና የኢትዮጵያ ጦር ግንቦት 1901 በሰይድ መሐመድ አብደላ ሐይላት ላይ በሰወስት አቅጣጫ ጥቃት ቢከፍትም በሶማሊያዎቹ ከመሸነፍ አላመለጠም።

ብሪታንያዎች ጥቅማቸዉን ለማስከበር ችግር ሲመጣባቸዉ፥ ከጠላታቸዉ ተወዳጅተዉ፥ ደም የተቃቡ ጠላቶችን አስተባብረዉ የሚፈልጉትን የማስፈፅም ችሎታቸዉን ግን ሶማሊያ ላይ በግልፅ ያስመሰከሩት ያኔ ነበር።ኋላም ለድል በቅተዋል።አሁንም በሶማሊያ ሰበብ የኢትዮጵያና የአሚሶም መሪዎች ግንኙነት ሻክሯል።የናይሮቢና የሞቃዲሾ መሪዎች ወዳጅነትም ወይዘሮ አኔተ ቬበር እንደሚሉት ወደ ግጭት እያመራ ነዉ።

«አዎ ሶማሊያ ዉስጥ ትልቅ ፖለቲካዊ ሥኬት አይታይም።በኬንያና በሞቃዲሾ መንግሥት መካካልም የመጋጨት አዝማሚያ ይታያል።»

ብሪታንያና ተባባሪዎቻቸዉ ሥለፈለጉ ግን የአዲስ አበባ፥ የአሚሶም መሪዎችም ልዩነት ዉዝግባቸዉን ትተዉ፥ የኬንያዉ ፕሬዝዳትም መከሰስ መጠርጠራቸዉ በይደርን አስቀርተዉ ነገ ከሞቃዲሾ መሪዎች ጋር ለንደን ላይ እኩል ይሰየማሉ።የጉባኤዉ ሒደትና ዉጤት አዘጋጆቹ እንዳሉት የሶማሊያን ችግር ለማቃለል መርዳት አለመርዳቱ በርግጥ ወደፊት የሚታይ ነዉ።

ሶማሊያ በርስ በርስ ጦርነት መዳከር ከጀመረች ወዲሕ ጅቡቲ፥ አዲስ አበባ፥ ካይሮ፥ ናይሮቢ እየተባለ አስራ-ዘጠኝ ጉባኤዎች ተደርገዋል።ጠቅላይ ሚንስትር ዴቪድ ካሜሩን ቀዳሚዎቻቸዉ ያሸጉበትን የሶማሊያን «ዶሴ» አዋራ አራግፈዉ ባለፈዉ የካቲት ያዘጋጁት ጉባኤ አዉሮጳ ዉስጥ የተደረገ-የመጀመሪያዉ፥ ለሶማሊያና ለአፍሪቃዉያን ግን ሃያ አንደኛዉ ነበር።

ካሜሩን ሃያ-አንደኛዉን ጉባኤ የሶማሊያን ፋይል ከመዝገብ ቤት ያወጡት ዩናይትድ ስቴትስና የአዉሮጳ ሕብረት ከ2009 ጀምሮ ለሶማሊያ የሽግግር መንግሥት እና ሶማሊያ ለሠፈረዉ የአፍሪቃ ጦር፥ በብዙ ሚሊዮነ የሚቆጠር ዶላር ካፈሰሱ በሕዋላ ነዉ።አሸባሪዎችንና የባሕር ላይ ወንበዴዎችን የሚወጋ ጦር፥ አደን ባሕረ-ሠላጤና ጅቡቲ ላይ ካሠፈሩ በሕዋላ ነዉ።

ብሪታንያ ባዶም ቢሆን ኤምባሲ የከፈተችዉ፥ለሁለተኛ ጊዜ ለነገ-ጉባኤ የጠራችዉ ደግሞ የሶማሊያ ቅምጥ የተፈጥሮ ሐብት ከፍተኛነቱ ከተረጋገጠ በኋላ ነዉ።አረቦች፥ ኢራኖች፥ ቱርኮች ሞቃዲሾ ዉስጥ እግራቸዉን ከሰደዱ በሕዋላ ነዉ።የለንደኑ ወኪላችን ድል ነሳ ጌታነሕ ከዚሕ ቀደም እንዳለዉ ቻይኖችን አካባቢዉን በሚያማትሩበት ወቅት ነዉ።


ዓለምን ረስታ፥ በምዕራቡ ዓለም ተረስታ በርስ በርስ ጦርነት ስትወደም ከሃያ-ዓመት በላይ ያስቆጠረችዉ ሶማሊያ የሐያሉን ዓለም ትኩረት ማግኘቷ በርግጥ ጥሩ ነዉ።ጥሩዉ ትኩረት ለሶማሌዎች እንዲጠቅም የሶማሊያ ፖለቲከኞችና የልብ ደጋፊዎቻቸዉ ደቡብ ሶማሊያ፥ ሶማሊላንድ፥ ፑንትላንድ፥ ወዘተ እየተባለ አራት ቦታ የተሸራረፈችዉን ሐገር ማቀራረብ፥ የዉጪዉን ግፊት በዘዴ እያለፉ ከጠመንጃዉ ዉጊያ ጎን ለጎን ድርድርን እንደአማራጭ ለመከተል ቢዘይዱ የተሻለ ዉጤት ማምጣቱ አይገድም።

NUR ZUR REDAKTIONELLEN NUTZUNG! A handout picture provided by the African Union-United Nations Information Support Team shows a Ugandan soldier serving with the African Union Mission in Somalia (AMISOM) standing at the back of an amoured fighting vehicle near a defensive position along the front-line in the Yaaqshiid District of northern Mogadishu, Somalia, 05 December 2011. In the face of a surge of car bombings and improvised explosive device (IED) attacks, the 9,700-strong African Union force continues to conduct security and counter-IED operations in and around the Somali capital. EPA/STUART PRICE / AU-UN IST PHOTO / HANDOUT HANDOUT EDITORIAL USE ONLY/NO SALES +++(c) dpa - Bildfunk+++ dpa 28561906
የአፍሪቃ ጦርምስል picture-alliance/dpa
African Union Mission in Somalia (AMISOM) combat engineers repair and grade a stretch of road leading to the town of Afgooye in Somalia's Lower Shabelle region, along the main route linking the fertile, agricultural region with the capital Mogadishu in this picture provided by African Union-United Nations Information Support Team taken January 24, 2013 and received by Reuters January 26, 2013. After years under the control of the Al-Qaeda linked group Al Shabaab, stretches of the economically important thoroughfare were virtually in-passable. Now, 7 months after the Shabaab were forced to flee following "Operation Free Shabelle", in which the Somali National Army, supported by AMISOM forces, liberated the Afgooye Corridor, the engineers have begun repairing the 4.5km (2.8 miles) stretch of road to increase ease and flow of traffic carrying people and produce to and from Mogadishu. REUTERS/AU-UN IST PHOTO/Stuart Price/Handout (SOMALIA - Tags: MILITARY POLITICS) ATTENTION EDITORS - THIS IMAGE WAS PROVIDED BY A THIRD PARTY. FOR EDITORIAL USE ONLY. NOT FOR SALE FOR MARKETING OR ADVERTISING CAMPAIGNS. THIS PICTURE IS DISTRIBUTED EXACTLY AS RECEIVED BY REUTERS, AS A SERVICE TO CLIENTS
የአፍሪቃ ጦርምስል picture-alliance/dpa
Photo taken September 22, 2012 shows AU soldiers from Uganda looking at some of the weapons recovered from members of Somalia's Al-Qaeda-linked Shebab after they gave themselves up to African Union Mission in Somalia (AMISOM) forces in Garsale, some 10km from the town of Jowhar, 80km north of the capital Mogadishu. Over 200 militants disengaged following in-fighting between militants in the region in which eight supporters of Shabaab were killed, including two senior commanders. The former fighters were peacefully taken into AMISOM's protection handing in over 80 weapons in the process, in a further indication that the once-feared militant group is now divided and being defeated across Somalia. Deputy Force Commander of AMISOM Operations, Brigadier Michael Ondoga said a number of militants have contacted the AU force indicating their wish to cease fighting and that they their safety is assured if they give themselves up peacefully to AMISOM forces. AFP PHOTO/ MOHAMED ABDIWAHAB (Photo credit should read Mohamed Abdiwahab/AFP/GettyImages)
የአፍሪቃ ጦር ድልምስል Mohamed Abdiwahab/AFP/Getty Images
A Somali woman who was displaced from her home village due to one of the harshest droughts affecting the region in the past 60 years, washes clothes near the bullet riddled wall of a mosque in a neighborhood of Somalia's capital Mogadishu on August 15, 2011. This neighborhood saw fierce fighting between armed extremist insurgents belonging to Al-Shebab and pro-government soldiers and fighters vying for power in the city. The Al-Shebab who until recently controlled part of this neighborhood left the city a few weeks ago. Many of the Somali's who were displaced by the famine affecting the region moved into the neighborhood and are now living in makeshift shelters among the ruins. Over 100,000 people have fled into Somalia's famine-hit and war-torn capital in the past two months in search of food, water and medicine. Some 12 million people in parts of Ethiopia, Djibouti, Kenya, Uganda and Somalia are in danger of starvation in the wake of the region's worst drought in decades. War-wracked Somalia is the country hardest hit by the Horn of Africa's drought, with five areas declared to be experiencing famine. AFP PHOTO/ROBERTO SCHMIDT (Photo credit should read ROBERTO SCHMIDT/AFP/Getty Images)
ምስል AFP/Getty Images
People walk around the remains of a damaged car at the scene of a car bomb explosion along the "Kilometre 4" road junction, south of the capital Mogadishu, May 5, 2013. A car bomb hit a convoy of cars carrying Qatari officials through the centre of Somalia's capital Mogadishu on Sunday, killing at least eight Somalis, officials said. REUTERS/Feisal Omar (SOMALIA - Tags: CIVIL UNREST DISASTER POLITICS)
ሞቃዲሾ -ሽብርምስል Reuters
WASHINGTON, DC - JANUARY 17: Secretary of State Hillary Clinton (R) shakes hands with Somali president Hassan Sheikh Mohamud during a news conference on January 17, 2013 in Washington, DC. Secretary Clinton announced that the United States would recognize the Somali government for the first time in over 20 years, since the shooting down in Mogadishu of two American Black Hawk helicopters. (Photo by Justin Sullivan/Getty Images)
እዉቅናምስል Getty Images

ነጋሽ መሐመድ
ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ