1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሶማሊያ ስደተኞች ከሳውዲ አረቢያ በግዳጅ መባረር

ዓርብ፣ ሐምሌ 30 2002

የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽን በእንግሊዘኛው ምህፃር UNHCR የሶማሊያ ስደተኞች ከሳውዲ አረቢያ በጅምላ በግዳጅ ወደ ሶማሊያ መባረራቸውን ለማስቆም የሚረዳ የመፍትሄ ሀሳብ ለሳውዲ አረቢያ መንግስት ማቅረቡን አስታወቀ ።

https://p.dw.com/p/OeFO
ምስል Bettina Rühl

በሳውዲ አረቢያና በባህረ ሰላጤው አገራት የUNHCR ተጠሪ ሚስተር ያኩብ አልሂሎ ፣ ለዶይቼቬለ በሰጡት ቃለ ምልልስ UNHCR ና የሳውዲ አረቢያ መንግስት የሶማሊያ ስደተኞችን ሁኔታ በጋራ እንዲያጣሩ የቀረበውን የመፍትሄ ሀሳብ የሳውዲ መንግስት በመርህ ደረጃ መቀበሉን ተናግረዋል ። ዝርዝሩን ሂሩት መለሰ አጠናቅራለች ።

ሂሩት መለሰ


አርያም ተክሌ