የሶማሊያዉ ፕሬዝዳት በዩናይትድ ስቴትስ
ረቡዕ፣ መስከረም 27 2002ማስታወቂያ
የሶማሊያዉ ፕሬዝዳት ሼኽ ሸሪፍ ሸኽ አሕመድ ዩናይትድ ስቴትስ ዉስጥ ከሚኖሩ ሶማሊያዉያዉያን እና ሶማሊያዉያን አሜሪካዉያን ጋር የሚያደርጉትን ዉይይት እንደቀጠሉ ነዉ።በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ለመገኘት ከሁለት ሳምንት በፊት ኒዮርክ የገቡት ፕሬዝዳት ሸርፍ በተለያዩ የአሜሪካ ግዛቶች እየተዘዋወሩ በየአካባቢዉ ለሚኖሩ የሶማሌ ተወላጆችና ወዳጆች ገለፃና ማብራሪያ አድርገዋል።የፕሬዝዳቱን ጉብኝትና በየስፍራዉ ያደረጉትን ዉይይት ያደራጁት እንደሚሉት ሸኽ ሸሪፍ አሜሪካ በሚኖሩት ሶማሊያዉያን ዘንድ ሰፊ ድጋፍና ተቀባይነት እያገኙ ነዉ።የዋሽንግተኑ ወኪላችን አበበ ፈለቀ ዝር ዝሩን አጠናቅሮታል።
አበበ ፈለቀ/ነጋሽ መሐመድ
ተክሌ የኋላ