የስፖርት ዝግጅት 09.11.15
ሰኞ፣ ጥቅምት 29 2008ማስታወቂያ
በቻይና ሻንጋይ ከተማ በተካሂደው በጎርጎሮሳዊው 2015 የቻይና ሻንጋይ ዓለም አቀፍ ማራቶን ሩጫ ውድድር የ19 አመቱ ኢትዮጵያዊ አትሌት ቶላ ሹራ 2 ሰአት 08 ደቂቃ 53 ሰከንድ በመግባት ሶስተኛ ሆኗል። ኬንያዊው አትሌት ፖል ኪፕቹምባ በ2 ሰአት 07 ደቂቃ 14 ሰከንድ በመጨረሽ ውድድሩን አሸንፏል ። ያለፈው አመቱ የውድድሩ አሸናፊ ደቡብ አፍሪካዊው ስትፍን ሞኩካ ደግሞ 2 ሰአት 07 ደቂቃ 40 ሰከንድ በመግባት ሁለተኛ ወጥቷል ። በሴቶች ተመሳሳይ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ሁለተኛ እና ሶስትኛ ሆነዋል አትሌት ለተብርሀን ሀይሌ 2 ሰአት ከ 28 ደቂቃ ከ 11 ሰከንድ በመገባት ሁለተኛ ራህማ ቱሳ 2 ሰአትከ 33 ደቂቃ 57 ሰከንድ በማስመዝገብ ሶስትኛ ደረጃ አግኝታለች ። ውድድሩን በአንደኝነት ያጠናቀቀችው የ31 አመትዋ ኬንያዊት አትሌት ሪል ኒግሪቱኪ ናት ። ውድድሩን በ2 ሰአት ከ26 ደቂቃ ከ23ሰከንድ ነው የጨረሰችው። ዝርዝሩን የለንደንዋ ዘጋቢያችን ሃና ደምሴ አዘጋጅታዋለች ።
ሃና ደምሴ
ኂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ