የስደተኞች ጫና ከጣሊያን ወደ ባልካን
ማክሰኞ፣ ጳጉሜን 3 2007ማስታወቂያ
ጀርመን 800 ሺህ ስደተኞችን ተቀብላ ከህብረተሰቡ ጋር ተዋህደው እንዲኖሩ ማድረጉ ይሳካልኛል ብላ እንደምታስብ ገልጣለች። የቀኝ አክራሪ ብሔርተኛ መንግሥት በሚመራት ሐንጋሪ ደግሞ በመዲናይቱ ቡዳፔስት ዋናው ባቡር ጣቢያ እና በተለያዩ ቦታዎች ስደተኞቹ እንግልት ሲደርስባቸውም ተስተውሏል። የጣሊያን መንግሥት በርካታ ስደተኞች መኖሪያ ቀዬያቸውን ጥለው የሚወጡባቸው ሃገራት ተለይተው ኹኔታቸው ሊጠና ይገባል ብሏል። ሕገ-ወጥ የስደተኞች አዘዋዋሪዎች ላይም ጠንከር ያለ ርምጃ እንዲወሰድ ጥሪ አስተላልፈዋል። የሮሙ ወኪላችን ተክለእዝጊ ገብረ እየሱስ ዘገባ አለው።
ተክለእዝጊ ገብረ እየሱስ
ማንተጋፍቶት ስለሺ
አዜብ ታደሰ