የስደተኞች ጎርፍ በፈረንሣይ
ቅዳሜ፣ መስከረም 24 2007ማስታወቂያ
ስደተኞች በሰሜን ፈረንሳይ የወደብ ከተማ ካላይ ከተማ ከምንጊዜውም በላይ በመጉረፍ ላይ ናቸው። ምክንያቱ ደግሞ ከእዚህች የወደብ ከተማ ወደ ታላቋ ብሪታንያ ለመግባት ርቀቱ ከ30 ኪሎ ሜትሮች ያለመብለጡ መሆኑ ተገልጿል። ልክ በድርጊት የተሞሉ ፊልሞች ላይ እንደሚሆነው ሁሉ ስደተኞች በሰፋፊ አውራ መንገዶች ላይ በፍጥነት በሚሽከረከሩ የጭነት መኪናዎች ላይ እየተሯሯጡ በአደገኛ ሁናቴ ሲጫኑ መመልከት የተለመደ ሆኗል። በአጠቃላይ በፈረንሣይዋ የካላይ ከተማ ስደተኞችን በተመለከተ ሁኔታዎች ከቀን ቀን እየተወሳሰቡ መምጣታቸው እየተነገረ ነው። ጊዮርግ ማቲያ ስ ስደተኞቹ ን በቦታው ተመልክቶ የላከውን ይልማ ኃይለ ሚካኤል እንደሚከተለው አቀናብሮታል።
ጊዮርግ ማቴስ/ይልማ ኃይለሚካኤል
አዜብ ታደሰ