የስዊድን ቴቪ ድረ-ገፅ ታገደ መባሉ
ሰኞ፣ መስከረም 14 2005ማስታወቂያ
የስዊድን መንግስት ቴሌቪዝን ድረገፅ ኢትዮጵያ ዉስጥ ከቅዳሜ ጠዋት አንስቶ መታየት እንዳይች ሆኖ መታገዱን የሚጠቁም ዘገባ ይፋ ሆኗል። እንደዘገባዉ ድረገፁ www.SVT.se የሚል ነዉ። SVT የተሰኘዉ ቴሌቪዥን ኢትዮጵያ ዉስጥ ከሽብርተኞች ጋ በመተባበር እንዲሁም ድንበር ያለ ይፋዊና ህጋዊ ፈቃድ አልፈዉ በመግባት የተከሰሱት እና ኋላ በዘንድሮዉ አዲስ ዓመት መባቻ ተለቀዉ ወደሀገራቸዉ የገቡትን ሁለት ጋዜጤኞች አነጋግሮ ዘገባ ማቅረቡ ተጠቅሷል። ድረገፁ ገጠመዉ የተባለዉ እክል እየተጠና እንደሆነም ዘገባዉ አመልክቷል። ይህን ዘገባ ተንተርሶ እንዲያጣራ መረጃዉን ያጋራነዉ ወኪላችን ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔርን ሸዋዬ ለገሠ በስልክ አነጋግራዋለች።
ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር
ሸዋዬ ለገሠ