የስነተዋልዶ ጤና ያገኘዉ ትኩረት12 ሰኔ 2004ማክሰኞ፣ ሰኔ 12 2004አምስት ሀገሮች በስነተዋልዶ ጤና ረገድ ያደረጉት ጥረት ባሳየዉ ተስፋ የአዉሮጳዉያን ዓመት የ2012ን የጤና ስኬት ሽልማት አገኙ። ኢትዮጵያ አንዷ ስትሆን፤ ማላዊ፣ ኔፓል፤ ሩዋንዳና የመንም ይገኙበታል። ኢትዮጵያ ከሰላሳ ሺህ በላይhttps://p.dw.com/p/15HyCምስል Fistula e.V.ማስታወቂያ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎችን በማኅበረሰቡ ዉስጥ በማሰማራት የቤተሰብ ምጣኔ ግንዛቤ እንዲኖርና የወሊድ መከላከያም በስፋት እንዲዳረስ ያደረገችዉ ጥረትም ለሌሎች ሀገሮች አርአያ ሊሆን እንደሚችል ተገልጿል። በ2207ዓ.ም የወጣ ጥናት ኢትዮጵያ ዉስጥ ለአንድ ሺህ ህዝብ 0,022 ሃኪም/ዶክተር፤ ለአንድ ሺህ ታማሚዎች ደግሞ 0,18 የአልጋ እንደሚገኝ ያመለክታል። ሸዋዬ ለገሠ አርያም ተክሌ