የስምጥ ሸለቆ የዉሃ አካላት
ረቡዕ፣ ጥር 18 2003ማስታወቂያ
የዉሃ ሰገነት የሚል ቅጽል የተሰጣት ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ በድርቅና በዉሃ እጥረት ትጠቃለች። የተፈጥሮ ሃብትን በአግባቡ መያዝ በቀጣይ ሊገጥም ከሚችል እንከንና እክል ያድናል። ዉሃ ለህይወት አስፈላጊነቱን ለመግለጽ ዉሃ ህይወት ነዉ ይባላል። ይህ ህይወት የሆነዉ ዉሃ በተፈጥሮ ከሚያስከትለዉ ጉዳት ባሻገር፤ ከአያያዝ ጉድለት ለህይወት መጥፋት ምክንያትም ይሆናል። ሲበከል፤ ስፍራዉ በደለል ሲሞላ፤ ሊሰጥ የሚችለዉ በጎ አገልግሎት ይስተጓጎላል። በስምጥ ሸለቆ የሚገኙት ሃይቆችም ሆኑ ወራጅ ወንዞች ጫና እንደበዛባቸዉ ያም ለችግር እያጋለጣቸዉ እንደሆነ ባለሙያዎች ያሳስባሉ። ዝርዝሩን ከጥንቅሩ ያድምጡ!
ሸዋዬ ለገሠ
ተክሌ የኋላ