የሴራልዮናዊው ተገን ጠያቂ አሟሟትና አወዛጋቢው ብይን
ሐሙስ፣ ጥር 7 2001ማስታወቂያ
ከጀርመንና ከጀርመን ውጭም የበርካታ የሰብዓዊ መብት ተከራካሪዎችን ትኩረት ስቦ የቆየው ይኽው ጉዳይ ከሃያ ሁለት ወራት የፍርድ ሂደት በኃላ ባለፈው ወር በፌደራዊ ክፍለ ሀገሩ ፍርድ ቤት ብይን ተሰጥቶበታል ። ፍርድ ቤቱ በዚሁ ብይን በሰውነት ላይ ለሞት የሚያበቃ ጉዳት በማድረስ እንዲሁም ህይወት በማጥፋት ክስ ከቀረበባቸው ፖሊሶች በአንዱ ላይ የገንዘብ ቅጥት ሲወስን ሌላኛውን ደግሞ ጥፋተኛ አይደለም ሲል በነፃ አሰናብቷል ።