የሳዴክ የመሪዎች ጉባዔ ፍጻሜ
ረቡዕ፣ ነሐሴ 12 2002ማስታወቂያ
መሪዎቹ በዚሁ ጉባዔ ላይ የድርጅታቸውን ሰላሳኛ የምስረታ ዓመትንም አክብረዋል። ጉባዔው በአስራ አራቱ የሳዴክ አባል ሀገሮች መካከል የኤኮኖሚውን ትብብር የማሳደግ ዓላማ ይዞ የተነሳ ነበር። በአባል ሀገራት ማዳጋስካር የቀጠለው የፖለቲካ ውዝግብ እና በዚምባብዌ የተደረሰው የስልጣን መጋራት ስምምነት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ያልሆነበት ድርጊትም ጉባዔው ትኩረት ያሳረፈባቸው ሌሎች ጉዳዮች ነበሩ።
አርያም ተክሌ
ነጋሽ መሀመድ