1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የውጡልኝ አዋጅ ዳግም ተራዘመ

ረቡዕ፣ ሐምሌ 19 2009

ህገ ወጥ የሚባሉ የውጭ አገር ዜጎች ሳውዲ አረብያን ለቀው የሚወጡበት ጊዜ ካለፈዉ ሰኞ ጀምሮ ለተጨማሪ አንድ ወር ዳግም ተራዝሟል።

https://p.dw.com/p/2hBYI
Rückkehrer Äthiopien Saudi Arabien Riad
ምስል DW/S.Sibiru

የሳውዲ አረብያ የውጡልኝ አዋጅ ዳግም መራዘሙ

ሳዑዲ አረብያ የመኖሪያ  ፈቃድ የሌላቸው የውጭ ዜጎች ከሀገርዋ እንዲወጡ ያስቀመጠችውን ቀነ ገደብ ለሁለተኛ ጊዜ አራዘመች። በጅዳ-ሳዑዲ አረብያ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽህፈት ቤት በአምደ መረቡ ባሰራጨው ማስታወቂያ  ህገ ወጥ የሚባሉ የውጭ አገር ዜጎች ሳውዲ አረብያን ለቀው የሚወጡበት ጊዜ ካለፈዉ ሰኞ ጀምሮ ለተጨማሪ አንድ ወር ዳግም መራዘሙን ገልጧል። ቆንስላው ወደ ሀገራቸው መመለስ የሚፈልጉ ኢትዮጵያውያን የጉዞ ሰነድ እና ቲኬት እንዲያዘጋጁ ጠይቋል። ዳግም ስለተራዘመው ስለዚሁ አዋጅ ጅዳ የሚገኘውን ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክን በስልክ አነጋግሬዋለሁ።

ነብዩ ሲራክ

ኂሩት መለሰ

ነጋሽ መሐመድ