1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሳውዲ ርዳታ ለጋዛ ውጊያ ሰለባዎች

ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 28 2001

ፍልስጤማውያንና እስራኤል እጅግ ለብዙ ዓመታት በዘለቀው ውዝግባቸው እአአ ከ1967ዓም ወዲህ እንዲህ እንዳሁኑ የጠነከረ ውጊያ ሲያካሂዱ ያለፉት አስራ ሁለት ቀናት በጋዛ የቀጠለው ውጊያ የመጀመሪያው መሆኑ ነው።

https://p.dw.com/p/GSy7
ሰሜን ጋዛ ከእስራኤል የአየር ጥቃት በህዋላ
ሰሜን ጋዛ ከእስራኤል የአየር ጥቃት በህዋላምስል AP

ታዛቢዎች ከልክ ያለፈና ያልተመጣጠነ ባሉት የእስራኤል የአየር፡ የምድር እና የባህር ጥቃት ከአክራሪው የሀማስ ድርጅት ዒላማዎች ጎን በርካታ ሴቶች፡ ህጻናትና ሽማግሌዎችም ተጠቂዎች ሆነዋል። ውጊያው በጋዛ አሳሳቢ ሰብዓዊ ችግር በመፍጠሩ የቆሰሉትን የማከሙ ተግባር ይበልጡን አዳጋች እንደሆነባቸው የሀኪም ቤቶች ሰራተኞች ሲገልጹ ይሰማል። የሳውዲ ዐረቢያ መንግስት፡ ወኪላችን ነቢዩ ሲራክ እንደገለጸው፡ ይህንኑ ችግር ለማቃለል በማሰብ ለሀኪም ቤቶች እገዛ የሚሆን ርዳታ ልኮዋል።