የሳምንቱ የስፖርት ዝግጅት
ሰኞ፣ መስከረም 13 2006ማስታወቂያ
ከአፍሪቃ ለዓለም የእግር ኳስ ዋንጫ ውድድር ፤ ከ 10 ሩ የሚያልፉት 5 ቡድኖች የሚታወቁት በመጪው ጥቅምትና ኀዳር በሚካሄዱ የደርሶ መልስ ግጥሚያዎች ነው። ኢትዮጵያ የደረሳት ዕጣ ፤ ከናይጀሪያ ጋር ሲሆን፤ ከወዲሁ፣ ከሁለቱም ወገን ዝግጅትን በተመለከተ አስተያየቶች ይሰነዘራሉ። የኢትዮጵያ ቡድን ፤ የጨዋታ ጥበብ አያንሰውም ፤ ያም ሆኖ የአቅም ጥንካሬ ፣ ስልት የመቀያየር ብልሃትና «ዲሲፕሊን» ግን እንደሚያሻው ፣ ደቡብ አፍሪቃ ውስጥ ፤ በአፍሪቃ ዋንጫ ፤ ቡድኑ ከናይጀሪያ ጋር ያካሄደውን ጨዋታ የሚያስታውሱ አንዳንድ ታዛቢዎች ይናገራሉ። ይህን፤ አሠልጣኝ አቶ ሰውነት አሳምረው ስለሚያውቁት ፤ ቡድኑን በሚገባ እንደሚያዘጋጁት ይታሰባል። አሁን በቀጥታ ወደ ሳምንታዊው የአስፖርት ዘገባ እንሸጋገር።
ሃይማኖት ጥሩነህ
ተክሌ የኋላ