የሱማሊያ የሽግግር መንግስት የከፈተው ጉባኤ30 ነሐሴ 2003ሰኞ፣ ነሐሴ 30 2003የሱማሊያ የሽግግር መንግስት ህጋዊ የስልጣን ዘመን ከአንድ ወር በፊት ነበር የሚያበቃው። ነገር ግን ፕሬዚዳንት ሼክ ሸሪፍ አህመድ የሽግግር መንግስታቸዉን የህጋዊነት ጊዜ ለአንድ አመት ሊያራዝም የሚያስችለዉን ዉል ካምፓላ ላይ ባለፈዉ ሰሞን ተፈራርመዋል።https://p.dw.com/p/Rk2Mምስል dapdማስታወቂያይህ ሁኔታ ግን ሁሉንም ወገኖች እኩል አላስደሰተም። በጦርነት እና በረሀብ የተጠቃችው አገር ሶማሊያ የተሻለና የተረጋጋ መንግስት ለማቋቋም እንድትበዋ ከትናንት ጀምሮ ለ ሶስት ቀናት የሚቆይ ጉባኤ ሞቃድሾ ላይ ተከፍቷል። ልደት አበበ ሞቃዲሾ የሚገኘውን የዶይቸ ቬለ ኪስዋኺሊ ክፍል ዘጋቢ ፤ ሁሴይን አዌይስን በጉዳዩ ላይ አነጋግራ የሚከተለውን ዘገባ አጠናቅራለች። ልደት አበበ