የርዕዮት ክስና የጠበቃዋ ተቃዉሞ
ረቡዕ፣ ጥር 1 2005ማስታወቂያ
የጋዜጣ አምደኛ ርዕዮት ዓለሙ በአሸባሪነት ወንጀል የተበየነባት ቅጣት እንዲሠረዝ ለኢትዮጵያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሠበር ሰሚ ችሎት ያቀረበችዉን አቤቱታ ችሎቱ ዉቅድቅ አደረገዉ።ርዕዮት ዓለሙ ከዚሕ ቀደም የበታች ፍርድ ቤት አስራ-አራት ዓመት እስራትና የገንዘብ መቀጮ በይኖባት ነበር።ይግማኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ግን ቅጣቱን ወደ አምስት-ዓመታት እስራት ዝቅ አድርጎታል።ርዕዮት ዓለሙ ለሰበር ሰሚዉ ችሎት አቤት ያለችዉ የአምስት ዓመቱ እስራትም የሕግ አተረጓገም ክፍተት አለበት በሚል ነበር።ትናንት አዲስ አበባ ያስቻለዉ ሰበር ሰሚ ፍርድ ቤት ግን አቤቱታን ዉድቅ አድርጎታል።የርዕዮት ጠበቃ የችሎቱን ዉሳኔ አልተቀበለቱም።ዩሐንስ ገብረ እግዚ አብሔር ዝር ዝር ዘገባ ልኮልናል።
ዩሐንስ ገብረ እግዚ አብሔር
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ