የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ የእሥራኤል ጉብኝት19 ግንቦት 2006ማክሰኞ፣ ግንቦት 19 2006የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ በመካከለኛው ምሥራቅ ያካሄዱትን የሦስት ቀናት ጉብኝት አጠናቀው ወደ ቫቲካን ተመለስዋል። ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ ጉብኝታቸውን የጀመሩት ባለፈው ቅዳሜ በዮርዳኖስ ነበር። ከዚያም በነጋታውhttps://p.dw.com/p/1C7nVር/ሊ/ጳጳሳቱ የእሥራኤል መሪዎችን ሲሰናበቱምስል Getty Imagesማስታወቂያ እሁድ ወደ ፍልሥጤማውያን ራስ ገዝ አስተዳደር በማምራት በቤተልሔም የስድስት ሰዓታት ቆይታ አድርገው፣ ትናንት እሥራኤልን ጎብኝተዋል። ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ በዮርዳኖስ፣ በፍልሥጤማውያን ራስ ገዝ አስተዳደር እና በእሥራኤል ቆይታቸው የሶርያ ጦርነት፣ እንዲሁም፣ የእሥራኤል እና የፍልሥጤማውያን ውዝግብ ስለሚያበቃበት ሁኔታ አንስተዋል። ግርማው አሻግሬ አርያም ተክሌ ተክሌ የኋላ