የምግብ ርዳታ ፈላጊው ቁጥር ይጨምራል መባሉ
ማክሰኞ፣ ኅዳር 28 2008ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ አደጋ መከላከያ እና ዝግጁነት መስሪያ ቤት ኃላፊ አቶ ምትኩ ካሳ ትናንት እንደገለጹት፣ ለጋሽ ሃገራት ለመስጠት የገቡትን የምግብ ርዳታ ባለማቅረባቸው የኢትዮጵያ መንግሥት ከራሱ፣ ለችግር ጊዜ ካከማቸው ምግብ በማከፋፈል ላይ ይገኛል። እንደ አቶ ምትኩ ገለጻ በድርቁ ሰበብ እስካሁን አንድም የሰው ሕይወት አልጠፋም። ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ደመቀ መኮንን እንደሚገምቱት፣ ድርቁ እስከ ጎርጎሪዮሳዊው 2016 ዓም ድረስ የሚቀጥል ሲሆን፣ የትራንስፖርት እና የምግብ አቅርቦት እጥረት ዓቢይ እንቅፋቶች ደቅነዋል። ኢትዮጵያ ከ50 ዓመት ወዲህ በወቅቱ ከፍተኛ ድርቅ እንደገጠማት እና በዚሁ ሰበብ የተፈጠረውን ችግር ለመቋቋምም 1,4 ቢልዮን ዶላር ርዳታ እንደሚያስፈልጋት የግብረ ሰናዩ ድርጅት «ሴቭ ዘ ችልድረን» የኢትዮጵያ ቢሮ ኃላፊ ጆን ግራሀም አስታውቀዋል።
አርያም ተክሌ
ሂሩት መለሰ